Saturday, 22 October 2022 14:14

የሰላም ድርድሩ የፊታችን ሰኞ በደቡብ አፍሪካ ይደርጋል ተብሎ ይጠበቃል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በደቡብ አፍሪካ ይደረጋል የተባለው የሰላም ድርድር የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 14/2015 ዓ.ም ይካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል፡፡
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የሰላም ድርድሩ በሚመጣው ሰኞ በጁአንስበርግ እንዲደረግ ያቀረበውን ጥያቄ ሁለቱም ወገኖች ተቀብለውታል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ አማባሳደር ሬድዋን ሁሴን መንግስት ለሰላም ድርድር ከህብረቱ ኮሚሽን ጥሪ እንደደረሰው አመልክተው በመንግስት በኩል በድርድሩ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። የህወሐቱ ቃለ-አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው የአፍሪካ ህብረት በሚመራው የሰላም ድርድር ሂደት ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን ቀደም ሲል ማሳወቃቸውን ጠቅሰው አሁንም በተጠቀሰው ጊዜ ለድርድሩ ወደ ጁአንስበርግ ለማቅናት ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን መንግስት እየወሰደ ባለው የመከላከል እርምጃ ሳቢያ ከተለያዩ አካላት በቀረበበት የተሳሳተ ክስ ማዘናቸውን ገልፀው በሰላም ድርድሩ ላይ ለመሳተፍ ቁርጠኝነታችንን በድጋሚ እናረጋግጣለን ብለዋል፡፡
በመጪው ሰኞ በጁአንስበርግ ሊደረግ በታሰበው የሰላም ድርድር አሸማጋይ ይሆናሉ ከተባሉ 3 አፍሪካውያን አንዱ የሆኑት የኬንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ከድርድሩ እራሳቸውን ማግለላቸውን እንዳገለገሉ ይታወሳል፡፡  


Read 11050 times