Print this page
Saturday, 15 October 2022 10:56

“ዲጂታል ፋይናንስ ኢትዮጵያ ሾውኬዝ” ረቡዕ ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ዲጂታል የክፍያ ስርዓትን የሚከተሉ ከ40 በላይ ተቋማት የሚሳተፉበት “ዲጂታል ፋይናንስ ኢትዮጵያ 2022 ሾውኬዝ” የፊታችን ረቡዕ ጥቅምት 9 ቀን 2015 ዓ.ም በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ይከፈታል፡፡
“The Digital Financial Services Working Group” በተሰኙ ቡድኖች  የተዘጋጀውና በተባበሩተ መንግስታት የካፒታል ፈንድ (UNCDF) የሚደገፈው ይሄው ሾውኬዝ፤ ሶስት ዋና ዋና አላማዎች ያሉት ሲሆን እነዚህም ትብብርና ኔትወርክ መፍጠር፤ የዘርፉን ተዋንያንና የመንግስት አካላትን እርስ በእርስ በማገናኘት በዘርፍ ዙሪያ እንዲወያዩና በሚያጋጥሙ ችግሮች ላይ የመፍትሄ ሀሳብ በማፍለቅ  ዲጂታል ገበያው እንዲሳለጥ ማድረግ እንዲሁም ስለ ዲጂታል ፋይናንስ የማህበረሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ እንደሆኑ የሥራ ቡድኑ ዋና ሊቀ መንበር አቶ ዩሴፍ ክብረት ተወካይ ናኤል ሀይለ ማርያም ተናግረዋል፡፡
ባለፈው ረቡዕ ከሰዓት በኋላ በአዋሽ ባንክ ዋናው መሥሪያ ቤት አውደ ርዕዩን አስመልክተው አዘጋጆቹ በሰጡት መግለጫ፤ ይህ ዓለም አቀፍ አውደርዕይ በዋናነት የተዘጋጀው የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ 2025 አጀንዳንና የብሄራዊ ባንክን የዲጂታል ክፍያ ስትራቴጂ መሰረት በማድረግ ሲሆን በአውደ ርዕዩ ላይ ባንኮች፤ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትና በአጠቃላይ በዲጂታል የአሰራር ስርዓት ላይ የተሰማሩ ከ40 በላይ ተቋማት  ይሳተፋሉ ብለዋል።  ጥቅምት 9 እና 10 በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል በሚካሄደው አውደርዕይ ላይ ተቋማቱ አገልግሎታቸውን ለእይታ የሚያበቁ ሲሆን በዘርፉ ላይ የተሰማሩ ተቋማት አመራሮች ፤የመንግስት የስራ ሀላፊዎችና ባለድርሻ አካላት የፓናል ውይይት እንደሚያደርጉና የስራ ትስስሮች እንደሚፈጠሩም አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ የአውደርዕይ መግቢያ በነፃ ሲሆን በሁለቱ ቀናት ህብረተሰቡ አውደርዕዩን በነፃ እንዲጎበኝ አዘጋጆቹ ጋብዘዋል፡፡

Read 11303 times
Administrator

Latest from Administrator