Saturday, 03 September 2022 13:40

አፍሪካ ቴክ ኤክስፖ የፊታችን ረቡዕ ይከፈታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ጆርካ ኢቨንት ኦርጋናይዘር ከATX ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የአፍሪካ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ (አፍሪካ ቴክ ኤክስፖ) የፊታችን ረቡዕ ጳጉሜ 2 ከረፋዱ 4፡00 ጀምሮ በስካይላይት ሆቴል ይከፈታል።
በተከታታይ ለሶስት ቀናት በሚቆየው በዚህ ኤክስፖ በቴሌኮም፣ በፋይናንሻል ክፍያ፣ በማህበራዊ ሚዲያ፣ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ፣ በሶፍትዌር ግንባታ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በሶላር ቴክኖሎጂ፣ በሳይበር ደህንነት፣ በባንክና ኢንሹራንስ፣ በሜትር ታክሲ፣ በኮንሲዩመር ቴክኖሎጂና በግብርና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ዘርፎች የተሰማሩ ኩባንያዎች እንደሚሳተፉበት ታውቋል፡፡
 መንግስት ለቴክኖሎጂው ዘርፍ የሰጠውን ልዩ ትኩረት ታሳቢ በማድረግና ይህንንም  ፖሊሲ ውጤታማ ለማድረግ እንደተዘጋጀ በተነገረለት በዚህ ዓለም አቀፍ ኤክስፖ፤ በርካታ የሀገር ውስጥና የውጪ ኩባንያዎች እንደተሳተፉበትና በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት አዘጋጁ ጆርካ ኢቨንት ኦርጋናይዘር አስታውቋል፡፡
በኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርና በኢንቨስትመንት ኮሚሽን እውቅናና አድናቆት የተቸረው  የቴክኖሎጂ ኤክስፖ፤ በእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በሀገር ገፅታ ግንባታ፣ በኢኮኖሚ ግንባታ እንዲሁም ለዜጎች የስራ ዕድል ፈጠራ አዎንታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥር ነው ተብሏል፡፡
በመክፈቻው ዕለትም ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከኢኖቬሽንና ቴክሎጂ ሚኒስቴር፣ ከቱሪዝም ሚኒስቴር ከኢንቨስትመንት ኮሚሽንና ከሌሎችም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተጋበዙ ሚኒስትሮችና ተወካዮች እንዲሁም የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች እንደሚገኙም ታውቋል።

Read 11928 times