Print this page
Saturday, 27 August 2022 12:12

አዲስ ተግዳሮት በአፍሪቃ ቀንድ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

አሌክስ ዴ ዎል የተባለ ፀሐፊ “አዲስ ተግዳሮት በአፍሪካ ቀንድ” በሚል ዐቢይ ርዕስ ሥር- “አፍሪካ ቀንድ እና ቀይ ባሕር”- በሚል ንዑስ ርዕስ የሚከተለውን አስፍሯል። ምንጊዜም የማይበርደው የአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ዛሬም ለያዥ ለገራዥ እንዳስቸገረ አለ።
የአፍሪካ ቀንድ በታሪክ ራሱን እንደ አንድ ክልል አረጋግጦ ተቀምጦ አያውቅም። በአካላዊና በሰብዓዊ መልክዐ-ምድር ረገድ እጅግ መጠነ- ሰፊ ሲሆን፣ የክርስቲያኑንም የሙስሊሙንም ህብረተሰብ በማይተናነስ ቁጥር የሚነካ ነው። ህዝቦቹ´ኮ አፍሪካ ከመካከለኛው ምሥራቅ እና ከሕንድ ውቂያኖስ፣ በቅርቡ ደግሞ ከአውሮፓና ከአሜሪካ የተሳሰረ ነው። ያም ሆኖ እንደ አፍሪካ  ቀንድ ህዝብ ራሱን አያይም። ይልቁንም የአፍሪካ ቀንድ ከግዛቱ ውጪ ባሉ ሰዎች ነው በቅጡ የሚገለጠው። በተለይም በዓለም ታላላቅ ኃይሎች እንደ ችግር ፈጣሪ እየተቆጠረች ነው። የዛሬዋ አፍሪካ ቀንድ አሳሳቢ አባዜ፣ በዓለም አቀፉ የሥልጣን ትግል የደምበኛና የአቅራቢ ዓይነት እንዳይሆን ነው። ያ ደግሞ የገዛ ራስዋ ያልሆነ ጣጣ ነው።
የአፍሪካ ቀንድ ዋንኛ ዕዳ መልክዐ ምድራዊ አቀማመጡ ነው። የስዊስ ካናል በ1869 እ.ኤ.አ ሲከፈት ቀይ ባሕር ከዋና ዋናዎቹ የንግድ ደም ስሮች አንዱ ሆነ። የዓለም ኃያላን መንግስታትም የባሕር መርከብ እንቅስቃሴ ደህንነት ጉዳይ ዋና ጉዳያቸው ሆነ እንጂ ውስጡን የማስተዳደሩ ነገር አላሳሰባቸውም ነበር። በግዛቱ አዲስ የጂኦ - ስትራቴጂ ፍላጎት ባደረ ቁጥር እንደ ሁልጊዜው ያንኑ ዓይነት ውጥረት ይከሰታል። ይሄ በ1950ዎቹ በስዊስ ካናል ላይ በቀዝቃዛው ጦርነት ጅማሮ ላይ ታየ። እንደገና ደግሞ በ1970ዎቹ የዐረብና እስራኤል ጦርነት ሊፋፋም አናቱ ላይ ሲደርስና በኃያላን ፍጭት፣ በምሥራቅ አፍሪካ ቀንድና በየመን ሲያጥጥ ፈጥጦ ወጥቷል።
ከዚያ የተከተለው እንግዳ የሆነ ታሪካዊ ሲላሲሎ ነው። አሊያም አፆለሌ ልንለው የምንችለው አዙሪት ነው! ለሩብ ምዕተ ዓመት ያህል የግዛቱ አገሮች የራሳቸውን አጀንዳ ሲያቀነቅኑ ነበር። ዓለም አቀፍ ፍላጎቱ ባይቆምም የስትራቴጂው ፋይዳ እየቀነሰ መጥቶ የሰብዓዊ ደህንነት -ማለትም እንደረሃብን ማቆምና ጅምላ ጭፍጨፋን መግታት አጀንዳ ሆኑ። ያም አሁን እያተለወጠ ነው። የኤደን ባሕረ-ሰላጤ ከአስርት ዓመታት በፊት፣ ለአጭር ጊዜ በሶማሊያ ድንበር በባህር ዘራፊዎች ስጋት ላይ ወድቆ ነበር።
አሁን ደግሞ የባሰ ቁም ስቅል የሚታይበት ጊዜ መጥቷል። የዐረባዊ ፔኒንዙላው አልቃይዳ የየመንን የተወሰነ የባሕር ዳርቻ ተቆጣጠረ። የመርከብ ኢንሹራንስ አሳሳቢ ነው። በሳውዲ የሚመራው የአገሮች ኅብረት፣ በየመኑ እርስ በርስ ጦርነት ጣልቃ መግባቱ አልቀረም። ሊፈረካከስ የደረሰውን ሁኔታ ይብስ ለማናጋት ለሱማሌ ተስፈንጣሪ ቡድኖች ገንዘብ ይረጫሉ። የኤርትራንም መነጠል ለማፍረስ የወታደራዊ ሰፈር ይመሰርታሉ።
የአዳዲስ ጦርነት መቀፍቀፍ ስጋት እያኮበኮበ ነው። የኢትዮጵያና የኤርትራ ግንኙነት ውጥረትና ወታደራዊ አየር እየነፈሰበት ነው። በወታደራዊ ንቅናቄ በተነሳሳች በአዲስ መልክ ልብ በገዛች ኤርትራና በተቆጣች ኢትዮጵያ መካከል የሚኖረው ጠብ መጫር ሊናቅ አይገባውም። ሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች ዓለማቀፋዊ ትኩረት እየሳቡ ነው፡-
አንደኛው- የባህር ደህንነት ጉዳይ ነው። ከሞላ ጎደል የአውሮፓና ኢስያ የንግድ እንቅስቃሴ በቀይ ባሕር ላይ የሚያልፍ ነው። በዓመት 700 ሚሊዮን ዶላር ያህል ነው። ቀላል አይደለም!
ሁለተኛው- በኃይል የተደገፈ ከባድ ጽንፈኝነት መኖሩ ነው- የአልሻባብ አደጋ የዋዛ አይደለም። የአፍሪካ ሕብረት ለዚህ የሰጠው ምላሽ የጸረ-ሽብርተኞች መቋቋሚያ ኃይል ነው። ያም በሰላም ጠባቂዎች ኃይል መልክ ነው።
እነዚህ አሸባሪዎችን ሲዋጉ በአንጻሩ ሳውዲና ኳታር ዋሐቢዝምን ለማስፋፋት የሙስሊም ጽንፈኝነትን ማጠናከሪያ ብር ያፈስሳሉ።
የመጨረሻና ሦስተኛው ጉዳይ ስደት ነው። ከሶርያውያንና ከአፍጋኖች ቀጥሎ ግፈኛ መንግስታቸውን በመሸሽ ከአገር የሚሰደዱና አውሮፓ የሚገቡ ህዝቦች ኤርትራውያን ናቸው። በተስፋ መቁረጥ የአውሮፓ ህብረት ለኤርትራ ዕርዳታ ይሰጣል። ቀቢፀ ተስፋ ነው ግን! ምንም ካለማድረግ ይሻላል ነው ነገሩ።
የአፍሪካ ኅብረት ይሄንን ስትራቴጂያዊ ገዋ መድፈን አለበት። የባህረ-ሰላጤውን ኅብረት ምክር ቤት ጋር አጋርነት  ፈጥሮ መንቀሳቀስ አለበት!

Read 1468 times
Administrator

Latest from Administrator