Saturday, 27 August 2022 11:04

በመቀሌ ከተማ በተመረጡ ወታደራዊ ተቋማት ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነውኃያላኑ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

 ህዝቡ ራሱን ከኢላማዎቹ እንዲያርቅ ጥሪ ቀርቧል

        የህወሓት ታጣቂ ቡድን የተኩስ አቁም ስምምነቱን በይፋ በማፍረስ የጀመረውና እስከአሁንም በዘለቀው ጦርነት ጉዳት ማድረስ መቀጠሉን የገለፀው የፌደራል መንግስት፤ በታጣቂ ቡድኑ ወታደራዊ ተቋሞች ላይ እርምጃ ሊወስድ መሆኑን አስታውቋል፡፡
በትግራይ ክልል ውስጥ በተለይም የታጣቂ ቡድኑ ወታደራዊ መሳሪያዎችና ማሰልጠኛዎች ባሉበት ስፍራዎች የሚኖሩ ወገኖች ራሳቸውን ከኢላማዎቹ እንዲያርቁም መንግስት መክሯል፡፡
በተያያዘ ዜና፤ የመንግስት  ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት፣ ዓለማቀፍ ማህበረሰብ፣ ህውሃትን ወደ ሰላም መንገድ እንደሚያመጣው ጥሪ ለሰላማዊ መንገድ እንዲያዘጋ ዓለማቀፍ ማህበረሰብ ህውሃትን ወደ ሰላም ለመንገድ እንዲያመጣው ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ይህ ካልሆነና ህውሃት በጥቃቱ ከቀጠለ መንግስት በህግ የተለበትን ግዴታ ለመወጣት ሲል ማንኛውንም እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ አስታውቋል። ጽ/ቤቱ ትናንት ባወጣው መግለጫ ላይ እንደተገለጸው፤ ህውሓት ለሰላም የተከፈቱ በሮችን ሁሉ በመዝጋት የመከላከያ ሃይሉ ይዞ በቆየባቸው ቦታዎች ላይ ጥቃትፐ
 እየፈጸመ መሆኑን ገልጾ አለማቀፉ ማህበረሰብ “ሁለቱ ወገኖች” ከሚል ፍርደ ገምድል  ጥሪ ተላቆ ህውሓት መንግስት ወደያዘው የሰላም አማራጭ እንዲመጣ ግፊት ያደርግ ዘንድ ጠይቋል።


Read 12587 times