Print this page
Saturday, 13 August 2022 00:00

በሸቀጦች ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ኢትዮጵያ በ3ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ሱዳን በ245.1 በመቶ የዋጋ ግሽበት ትመራለች አፍሪካን
             
       ከአፍሪካ ሃገራት በወቅታዊ የሸቀጦች የዋጋ ግሽበት ኢትዮጵያ በ3ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን ሱዳን ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆናለች፡፡ የአለም ባንክ ከሰሞኑ  ያወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው፡ በፖለቲካ ሁከትና  አለመረጋጋት ውስጥ  የምትናጠው ሱዳን፣ በ245.1 በመቶ የሸቀጦች የዋጋ ግሽበት አፍሪካን ትመራለች፡፡
በየጊዜው የሸቀጦች የዋጋ ግሽበት ቀውስ የማንጣት ዚምባብዌ ደግሞ፣ በ86.7 በመቶ  የዋጋ ግሽበት በሦስተኛ ደረጃ ላይተቀምጣለች። ኢትዮጵያ በ34.5 በመቶ የዋጋ ግሽበት በሦስተኛ ደረጃ ላይ  ስትገኝ፡፡  አንጎላ 23.9 በመቶ፣ ሴራሊዮን 17.3 በመቶ፣ ጋና 16.፣3 በመቶ፣ናይጀሪያ 16.1 በመቶ፣ደቡብ ሱደን 16 በመቶ፣ዘምቢያ 15.7 መቶ በማስመዝገብ እስከ 10ኛ  ያለውን ደረጃ ይዘዋል በቅድመ ተከተላው መሰረት፡፡
ከአፍሪካ ሃገራት በጣም ዝቅተኛ የሸቀጦች ዋጋ ግሽበት ያስመዘገቡ  አስር ሃራት ደግሞ ደቡብ ሱዳን፣ቤኒን፣ሲሸልሲ፣ ካሜሮን፣ ኤርትራ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ረፐብሊክ ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ ጋቦን ስዋዚላንድ እና ቻድ ናቸው፡፡
በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሸቀጦች ዋጋ ግሽበት የተመዘገበው በምግብና ምግብ ነክ ቁሳቁሶች እንዲሁም በግንባታ የግብአቶች ላይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡
ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ያስመዘገቡ ሃገራት የህዝባቸውን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል  ላይ መትጋት እንደለባቸው የዓለም ባንክ ሪፖርት አሳስቧል፡፡

Read 6704 times
Administrator

Latest from Administrator