Print this page
Thursday, 11 August 2022 09:38

ኢትዮጵያዊ ወኔ ሙሉ በሙሉ ግንባታውን አጠናቅቀን የልባችን እንደሚሞላ አልጠራጠርም - ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ -

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ተርባይን፣ በዛሬው ዕለት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀመረ።

ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ዝግጅት ነው፣  ሁለተኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው።

በታሪክ ውስጥ ማለፍና ታሪክ ሠርቶ ማለፍ የሚባሉ ሁለት ነገሮች አሉ፡፡ በታሪክ ውስጥ ማለፍ ዕድል፣ ታሪክ ሠርቶ ማለፍ ግን ዕድልም ድልም ነው፡፡ ይሄ ትውልድ በዓባይ ግድብ ጉዳይ ባለ ዕድልም ባለ ድልም ነው፤ ብለዋል ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፡፡

የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ካሉት 13 ተርባይኖች መካከል ዩኒት 9 የሚባለው ሁለተኛው ተርባይን፣ የተሳካ ተከላና ሙከራ ከተደረገ በኋላ ኃይል የማመንጨት ስራው እውን ሆኗል ተብሏል።

በዛሬው ዕለት ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት፣ 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡

ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ የእንኳን ደስ ያለን ንግግራቸውን የቋጩት የተሟላ ስኬትና እርካታ በመመኘት ነው፡-
እነሆ አሁን የሕዳሴ ግድብ ከንድፍ አልፎ፣ ግንባታው ተገባድዶ፣ ግዙፍ ውኃ በጉያው ይዞ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል። ዛሬ ዓባይ ተረት ሳይሆን የሚጨበጥ እውነት ነው፤ ከዘፈን-እንጉርጉሮ ወጥቶ ኢትዮጵያን በብርሃኑ ሊያደምቃት፣ ኃይል ሆኖ ሊያበረታት ከጫፍ ደርሷል። በፈጣሪ ርዳታና በኢትዮጵያዊ ወኔ ሙሉ በሙሉ ግንባታውን አጠናቅቀን የልባችን እንደሚሞላ አልጠራጠርም።  እንኳን ደስ ያለን!!

Read 5210 times
Administrator

Latest from Administrator