Saturday, 06 August 2022 11:55

“ንባብ ለህይወት” አውደ ርዕይ - በኤግዚቢሽን ማዕከል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  በኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከሰት ሳቢያ  ላለፉት ሁለት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው  “ንባብ ለህይወት” የመጻህፍትና የምርምር ተቋማት  አውደ ርዕይ፣ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የተከፈተ ሲሆን ለአምስት  ቀናት እንደሚቆይ ታውቋል፡፡
በዚህ 5ኛው “ንባብ ለህይወት”  አውደ ርዕይ ላይ ደራሲያን፣ የመጻህፍት አሳታሚዎችና አከፋፋዮች እንዲሁም የምርምር  ተቋማት እየተሳተፉ ሲሆን አዳዲስ መጻሕፍት በ20 በመቶ  ቅናሽ እየተሸጡ ነው ተብሏል፡፡
የ’ንባብ ለኢትዮጵያ’ ፕሮጀክት ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም ከበደ፤ በአውደ-ርዕዩ  በመቶዎች የሚቆጠሩ  ደራሲያን፤ የተለያዩ ተቋማትና ግለሰቦች ሥራዎቻቸውን ይዘው መቅረባቸውን ተናግረዋል።
በአውደ ርዕዩ ከ50 በላይ አዳዲስ መጻሕፍት እንደሚመረቁና የመጻሕፍት ውይይት እንደሚካሄድም ለማወቅ ተችሏል፡፡
አውደ-ርዕዩን፤ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጽሐፍት አገልግሎት፣ ከ’ንባብ ለህይወት’ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ነው ያዘጋጁት።


Read 17998 times