Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 13 October 2012 10:25

የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ805 ሚ. ብር ድጋፍ ሰጠ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ እድገትና የኢኮኖሚ ልማት ለማገዝ የ805 ሚ. ብር የገንዘብ ድጋፍ ሰሞኑን ሰጠ፡፡ የገንዘብ ድጋፉ የሀገሪቱን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማስፋፋትና ለማዘመን የሚውል ነው፡፡ የህብረቱ ድጋፍ ኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ እድገት ለማምጣት ያላትን አቅም መጠቀም እንድትችል ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ልማቷን እንድታፋጥን ያግዛታል ተብሏል፡፡ በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ልኡክ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አምባሳደር ዣቪያ ማርሻል፤ የአውሮፓ ህብረት የገንዘብ ድጋፍ፤ የኢትዮጵያ መንግስት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለመለወጥ እያደረገ ያለውን ጥረት በመደገፍ የኢንዱስትሪ እድገት እንዲፋጠን ያደርጋል ብለዋል፡፡

“ህብረቱ ባደረገው ድጋፍ አማካኝነት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት፣ የክህሎት ማጐልበቻ እና እያደገ ለመጣው የሠራተኛ ኃይል የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ የበኩሉን አስተዋፅኦ ማድረግ በመቻሉ ከፍተኛ ደስታ ይሰማኛል” ብለዋል - አምባሳደር ማርሻል፡፡ Transformation Triggering Facility  የተሰኘው የአውሮፓ ህብረት አዲሱ የልማት ድጋፍ በመንግስትና በግሉ ዘርፍ መካከል የበለጠ ውጤታማ ትብብር ለማስፋፋት፣ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ለማሳደግ ያግዛል፡፡ በተጨማሪም ፕሮጀክቱ የአውሮፓ ህብረትና የኢትዮጵያ የቢዝነስ ትምህርት ቤትና የአነስተኛና መካከለኛ ተቋማት የፈጠራ ማበልፀጊያ ማዕከል ለመገንባት ያስችላል ተብሏል፡፡

 

Read 3034 times Last modified on Saturday, 13 October 2012 10:37