Saturday, 11 June 2022 20:00

ታሪክ - ለልጆች

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 ውድ ልጆች፡- ከዚህ ታሪክ የምንማረው ቁምነገር፣ ማንንም በቅጡ ሳናውቅ ገጽታውን ብቻ አይተን ወደ ንቀትና ማሾፍ መግባት እንደሌለብን ነው። እጃቸው ላይ ልንወድቅ እንችላለንና፡፡

                   የወርቅ እንቁላል የምትጥለው ዶሮ

           ከዕለታት አንድ ቀን፣ አንድ ገበሬ በየቀኑ አንድ የወርቅ እንቁላል የምትጥል ዶሮ ነበረችው። እንቁላሉ ለገበሬውና ሚስቱ የዕለት ፍላጎታቸውን የሚያሟላ በቂ ገንዘብ ያስገኝላቸው ነበር። በዚህም ባልና ሚስቱ ለረዥም ጊዜያት ደስታቸውን እያጣጣሙ ኖሩ፡፡
አንድ ቀን ገበሬው እንዲህ ሲል አሰበ፤ “ለምን በቀን አንድ የወርቅ እንቁላል ብቻ እናገኛለን? ሁሉንም የወርቅ እንቁላሎች በአንዴ አውጥተን ለምን ብዙ ገንዘብ አናገኝም?”
ገበሬው ይህን ሃሳቡን ለሚስቱ አማከራት። ሚስቱም ሳታቅማማ ሃሳቡን ተቀበለች፡፡
ከዚያም በነጋታው ዶሮዋ የወርቅ እንቁላሏን ስትጥል፣ ገበሬው የተሳለ ቢላዋ ይዞ እየጠበቃት ነበር። ወዲያው አረዳትና እየተጣደፈ ሆዷን ከፈተው፤ የወርቅ እንቁላሎች  በገፍ አገኛለሁ በሚል ተስፋ። ሆዷን ሲከፍተው ግን ከአንጀትና ከደም በቀር ምንም አላገኘም፡፡
ይሄኔ በጅልነቱ የፈጸመውን ስህተት ተገንዝቦ፣ ከእጁ መዳፍ ላመለጠው ሃብት ማልቀስ ጀመረ። ገበሬውና ሚስቱ ከቀን ወደ ቀን ይበልጥ እየደኸዩ መጡ። ያጡ የነጡ ድሆችም ሆኑ።  አይ መጃጃል! ያሳዝናል!
ልጆች፡- ከዚህ ታሪክ የምንማረው ቁምነገር፣ በደንብ ሳናስብ፣ ሳናገናዝብና ሳንመክር  ምንም ድርጊት መፈጸም እንደሌለብን ነው። ስግብግብነትም ለጥፋት እንደሚዳርግ ከገበሬው ተምረናል፡፡


Read 1430 times