በትምባሆ ልማት 600 ሚ. ዛፍ፣ 200 ሺህ ሄክታር መሬትና 22 ቢ. ቶን ውሃ ይባክናል
በመላው አለም በየአመቱ ከ8 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በትምባሆ ምክንያት ለሞት እንደሚዳረጉና አብዛኞቹ ሞቶች የሚከሰቱትም በአለማችን ከሚገኙ ትምባሆ አጫሾች መካከል 80 በመቶው በሚገኙባቸው መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው አገራት መሆኑን ሰሞኑን የወጣ አለማቀፍ ሪፖርት አመልክቷል፡፡
ትምባሆ በአብዛኛው የሚለማው መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው አገራት መሆኑንና በአገራቱ ለምግብ ሰብሎች ልማት ይውል የነበረ ከፍተኛ መጠን ያለው ሃብት እንደሚባክን የጠቆመው የአለም የጤና ድርጅት ያወጣው አለማቀፍ ሪፖርት፣ በትምባሆ ልማት ሳቢያ በመላው አለም በየአመቱ 600 ሚሊዮን ያህል ዛፎች እንደሚጨፈጨፉ፣ 200 ሺህ ሄክታር መሬት እና 22 ቢሊዮን ቶን ውሃ እንደሚባክንም አመልክቷል፡፡
ከትምባሆ ጋር በተያያዘ በየአመቱ ወደ አየር የሚለቀቀው በካይ ካርቦንዳይኦክሳይድ 84 ሚሊዮን ቶን ያህል እንደሚደርስና የትምባሆ ምርቶች ከ7000 በላይ መርዛማ ኬሚካሎችን የያዙ እንደመሆናቸውና ተረፈ ምርታቸው ብዙ እንደመሆኑ በአካባቢ ብክለት ሚናቸው ከፍ ያለ እንደሆነም አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል