Wednesday, 18 May 2022 16:03

የውሃ አገልግሎት ክፍያ በቴሌብር ተግባራዊ ተደረገ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮ ቴሌኮም እና ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በተቀናጀ ደራሽ የክፍያ ሥርዓት አማካኝነት የውሃ አገልግሎት ሰጪ መሥሪያ ቤቶች የወርሃዊ አገልግሎት ክፍያን በቴሌብር ለመፈጸም የሚያስችል ስትራቴጂያዊ የአጋርነት ስምምነት ተደርጓል፡፡
በዛሬው ዕለት ግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም በሐረሪ፣ ፍኖተ ሰላም፣ እንጅባራ፣ ደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች የሚገኙ የቴሌብር ደንበኞች የውሃ አገልግሎት ክፍያቸውን በተቀናጀ ደራሽ የክፍያ ሥርዓት አማካኝነት በቴሌብር ለመፈጸም ይችሉ ዘንድ ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ስምምነት በመፈጸም አገልግሎቱን ተግባራዊ አድርገዋል፡፡


በዚህ ስምምነት መሠረት፤ የውሃ አገልግሎት ሰጪ መሥሪያ ቤቶች በተቀናጀ ደራሽ የክፍያ ሥርዓት አማካኝነት የደንበኞቻቸውን ወርሃዊ ሂሳብ በቴሌብር ለመሰብሰብ የሚያስችላቸው ይሆናል ተብሏል፡፡
#ይህ አሰራር የማህበረሰባችንን የዲጂታል ክፍያ ተጠቃሚነት ፍላጎት ለማሳደግ፣ በጥሬ ገንዘብ የሚደረገውን ግብይት ለመቀነስና የቢዝነስ መረጃዎችን ፍሰት በቀላሉ ለማወቅና ለማሻሻል ትልቅ ፋይዳ የሚኖረው ይሆናል፡፡; ብሏል፤ ኢትዮ ቴሌኮም በመግለጫው፡፡
የቴሌብር አገልግሎት ከተጀመረ ባለፈው ሳምንት አንድ ዓመት የሞላው ሲሆን እስካሁን 19 ሚሊዮን ደንበኞችን እንዳፈራ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 14643 times