Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 06 October 2012 13:30

“ናዋዡ ምሁር” መፅሐፍ ረቡዕ ይመረቃል “በራማ ሸለቆ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በጋዜጠኛና ደራሲ የምወድሽ በቀለ የተዘጋጀው “ናዋዡ ምሁር” የእውነተኛ ታሪክ መፅሐፍ በመጪው ረቡዕ ከቀኑ 10 ሰዓት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡ 160 ገፆች ያሉት መፅሐፍ ለሀገር ውስጥ በ30 ብር ለውጭ ገበያ ደግም በ10 የአሜሪካ ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡ የ“ፖሊሲና ርምጃው” ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረችው የምወድሽ፤ የኢትዮጵያ ሴት ደራስያን ማህበር ፕሬዚዳንት ስትሆን ካሁን ቀደም ለሕትመት ካበቃቻቸው መፃሕፍት መካከል “የባከነ ጊዜ”፣ “አብዮታዊ ግጥሞች”፣ “እብዷ በለጠች”፣ “ፍቅር የጠማቸው” እና “ዋጊኖስ” ይገኙበታል፡፡

በሌላም በኩል የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ተማሪ የሆነችው ውዳሴ ፈረደ ተገኘ “በራማ ሸለቆ” የተሰኘ የመጀመርያ የግጥም መፅሐፏን ለንባብ አበቃች፡፡ በ104 ገፆች የተካተቱት 108 ግጥሞች፤ ደራሲዋ ላለፉት አስር ዓመታት የፃፈቻቸው እንደሆኑ ታውቋው፡፡ ከብር በላይ ዋጋ አስከፍሎኛል ያለችው “አቤኔዘር የሕፃናት ማሳደጊያ” ሠራተኛ ውዳሴ ሁለት ሺህ ቅጂ ለማሳተም 21ሺህ ብር መክፈሏን ለአዲስ አድማስ ገልፃለች፡፡ በፋር ኢስት ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማህበር የታተመው መፅሐፍ፤ ለሀገር ውስጥ ገበያ በ25 ብር ለውጭ ገበያ ደግሞ በ10 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡

 

Read 3442 times Last modified on Saturday, 06 October 2012 13:34