Tuesday, 03 May 2022 00:00

የዩክሬን ጦርነት በግማሽ ክ/ዘመን ያልታየ የዋጋ ንረት ያመጣል ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ሩስያ በዩክሬን የከፈተችው ጦርነት በመላው አለም እ.ኤ.አ ከ1970ዎቹ ወዲህ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ የሸቀጦች አቅርቦት እጥረትና የዋጋ ንረት ሊያስከትል እንደሚችል የአለም ባንክ ከሰሞኑ ባወጣው ሪፖርት አስጠንቅቋል፡፡
የሁለቱ አገራት ጦርነት በመላው አለም ከተፈጥሮ ጋዝ እስከ ስንዴ እና ጥጥ በተለያዩ አይነት ምርቶች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ሊያስከትል እንደሚችል የተነበየው ባንኩ፣ ጦርነቱ እስካሁን ያስከተለው የዋጋ ጭማሪ በአለማችን ከፍተኛ የሆነ ኢኮኖሚያዊና ሰብዐዊ ጫና እያደረሰ እንደሚገኝም ማመልከቱንም ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የምግብ እህሎች ዋጋ ባለፉት 60 አመታት ከፍተኛው ደረጃ ላይ መድረሱን የጠቆመው ባንኩ፣ በቀጣይም በርካታ የምግብ እህሎች ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ያሳያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና የስንዴ ዋጋ በ42.7 በመቶ፣ የገብስ ዋጋ በ33.3 በመቶ፣ የዘይት ዋጋ በ29.8 በመቶ ያህል ሊጨምር እንደሚችል ነው በትንበያው የገለጸው፡፡
የዋጋ ጭማሪው በተለይም በድህነት ውስጥ የሚገኙ የአለማችን ዜጎችን ለከፋ አደጋ እንደሚያጋልጥ የጠቆመው የባንኩ ትንበያ፣ የሃይል ዋጋ በ50 በመቶ ያህል ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅና በተለይ ከፍተኛው የአውሮፓ የተፈጥሮ ጋዝ ዋጋ በእጥፍ  ይጨምራል ተብሎ እንደሚጠበቅም ያመለክታል፡፡

Read 7962 times