Saturday, 30 April 2022 13:01

አለማቀፉ ወታደራዊ ወጪ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ2 ትሪሊዮን ዶ. አልፏል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በፈረንጆች አመት 2021 አለማቀፍ ወታደራዊ ወጪ ካለፈው አመት የ0.7 በመቶ ጭማሪ በማሳየት 2.113 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱንና ወጪው ከ2 ትሪሊዮን ዶላር ሲያልፍ በታሪክ ይህ የመጀመሪያው መሆኑን ስቶክሆልም ኢንተርናሽናል ፒስ ሪሰርች ኢንስቲቲዩት የተባለው ተቋም ባወጣው አመታዊ ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
አለማቀፉ ወታደራዊ ወጪ ዘንድሮም ለ7ኛ ተከታታይ አመት ጭማሪ ማሳየቱን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ በአመቱ 801 ቢሊዮን ዶላር ያወጣችው አሜሪካ ከአለማችን አገራት መካከል ከፍተኛውን ወታደራዊ ወጪ ያወጣች ቀዳሚዋ አገር ስትሆን፣ ቻይና በ293 ቢሊዮን ዶላር፣ ህንድ በ76.6 ቢሊዮን ዶላር እንደሚከተሉም ያሳያል፡፡
በአመቱ አሜሪካ ወታደራዊ ወጭዋን በ1.4 በመቶ ያህል ብትቀንስም ቻይና በበኩሏ ለ27ኛ ተከታታይ አመት አምናም ወታደራዊ ወጪዋን በ4.7 በመቶ ያህል መጨመሯን ያሳየው ሪፖርቱ፣ በአመቱ በመላው አለም ከተመዘገበው አጠቃላይ ወታደራዊ ወጪ 62 በመቶውን ያወጡት አምስት የአለማችን አገራት አሜሪካ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ እንግሊዝና ሩስያ መሆናቸውንም ገልጧል፡፡
ከዩክሬን ጋር ጦርነት ውስጥ የገባችው ሩስያ በአመቱ ወታደራዊ ወጪዋን በ2.9 በመቶ በመጨመር 65.9 ቢሊዮን ዶላር ማድረሷን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ ዩክሬን በበኩላ 5.9 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ወጪ ማድረጓን ነው የሚያሳየው፡፡

Read 1759 times