የአዲስ አድማሱ አሰፋ ጎሳዬ፤ በዛሬዋ ቀን የካቲት 16 ቀን ተወለደ፡፡
*አንዳንዶች ለጥበብና ለጥበብ ባለሙያዎች በነበረው ፍቅርና መቆርቆር ያስታውሱታል፡፡
*አንዳንዶች በዕውቀት ወዳድነቱና አዳዲስ ሃሳቦችን ለመተግበር በነበረው ድፍረትና ትጋት ያነሱታል፡፡
*ብዙዎቹ ወዳጆቹ የትላልቅ ህልሞች ባለቤትና ባለራዕይነቱን አድንቀው ያወሳሉ፡፡
*ሌሎች በደግነቱ፣ በተጫዋችነቱና በሳቂታነቱ ሁሌም አይረሱትም፡፡
እኛ ደግሞ #እኔ ማወቄ የሚገባኝ ህዝቡ ሲያውቅ ነው; በምትለው ድንቅ አባባሉ
ስናስታውሰው እንኖራለን!!
ፈጣሪ ነፍሱን በአጸደ ገነት ያኑርለት!!