Print this page
Saturday, 22 January 2022 00:00

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋት 164.5 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አጥታለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ባለፈው የፈረንጆች ዓመት የኢንተርኔት ግንኙነትን  በማፈን ናይጀሪያና ኢትዮጵያ በቀዳሚነት በተጠቀሱበት ሪፖርት፣ ከሠሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሃገራት በዚሁ የአፈና ተግባራቸው በአጠቃላይ 1.93 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማጣታቸውን በተባበሩት መንግስታት ድጋፍ የሚደረግለት የአደጋ ጊዜ ምላሽ ፈንድ በሪፖርቱ አመልክቷል፡፡
ተቋሙ ባደረገው ጥናት፣ ከሠሃራ በታች ካሉ ሃገራት የኢንተርኔት አገልግሎትን ሆን ብሎ በማፈን ናይጄሪያ ቀዳሚ ስትሆን፤ ኢትዮጵያ በሁለተኛነት ተጠቅሳለች፡፡
እንደ ሪፖርቱ ከሆነ በ2021 በኢትዮጵያ ለ8 ሺህ 760 ሰዓታት ኢንተርኔት ሙሉ በሙሉ ዝግ መደረጉን ተከትሎ ሃገሪቱ ታገኛው የነበረውን 164.5 ሚሊዮን ዶላር አጥታለች፡፡
144 ሚሊዮን የኢንተርኔት ተጠቃሚ ዜጎች ያሏት ናይጀሪያ ደግሞ በዓመቱ ለ5 ሺህ  40 ኢንተርኔት በማቋረጥ 1.45 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷን ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡
በሃገራቱ ኢንተርኔትን ለማቋረጥ ምክንያት  ተብለው ከተጠቀሱት በዋናነት የፖለቲካ መብቶችን ለመገደብ የሚደረግ ጥረት ተጠቃሽ ሆኗል፡፡
ሃገራቱ ኢንተርኔትን በሚገድቡበት ምክንያት 69 በመቶ የመሰብሰብ መብትን ለማፈን፣29 በመቶ በምርጫ ጉዳይ የሃሳቦች መንሸራሸርን ለመገደብ እንዲሁም 29 በመቶ የፕሬስ ነፃነትን ለመገደብ በማሰብ መሆኑን የጠቆመው ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ  በትግራይ የአማፂያንን እንቅስቃሴ ለመገደብ ኢንተርኔት ማቋረጡን አመልክቷል፡፡
ኢንተርኔት ይገድባሉ ተብለው በሪፖርቱ ስማቸው ከተጠቀሱ ሃገራት መካከል  ደቡብ አፍሪካና ኬኒያም ይገኙበታል፡፡


Read 3487 times
Administrator

Latest from Administrator