Saturday, 15 January 2022 20:32

የህብረት ባንኩ “ህብር ታወር” ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ባለ 37 ፎቅ ህንጻው 2.8 ቢ.ብር ፈጅቷል

                ህብረት ባንክ አክስዮን ማህበር ሰንጋ ተራ አካባቢ ያስገነባውን ባለ 37 ወለል የዋና መስሪያ ቤት ህንጻ ህብር ታወር፣ ዛሬ ከረፋዱ 3፡00 ጀምሮ ይመረቃል። ለግንባታው 2.8 ቢሊዮን ብር የወጣበትና ግንባታው 6 ዓመት የወሰደው ህብር ታወር በባንኩ ላይ ከፍተኛ ለውጥና እድገት እንደሚያመጣም ነው የተገለፀው፡፡
የባንኩ ሀላፊዎች ከትላንት በስቲያ ረፋድ ላይ በዚሁ ታወር ላይ ምርቃቱን አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት፣ህንጻው ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ ፋሲሊቲዎች ያሉት ሲሆኑ ዘመናዊ በኮምፓስ የሚሰሩ 13 አሳንሰሮች፣ በሴንሰር የሚሰራ መብራትና ውሃ፣ ከ147 በላይ ካሜራዎች፣ የማይቋረጥ የሀይል አቅርቦት ቢዩልዲንግ ማኔጅመጀነት ሲስተም (BMS) የተገጠመለትና ሌሎችንም በርካታ አገልግሎት ያሟላ መሆኑን አስታውቀዋል። በመዲናችን አዲስ አበባ “የፋይናንስ ተቋማት በሚገኙበት ሰንጋ ተራ አካባቢ የተገነባው ይሄው ህንጻ፤ ለከተማዋ ልዩ ውበትን ከማላበሱም በላይ ትልቅ አልሞ ትልቅ ደረጃ መድረስ እንደሚችል ማሳያም ጭምር እንደሆነ ነው ዋና ስራ አስፈጻሚው የገለፁት፡፡
ህንጻው በተለያዩ ወለሎቹ የተለያዩ መጠን ያላቸው አዳራሾች፣ ካፊቴሪያዎችን  ዘመናዊ ጅምናዚሞችና ኩሽናዎችን ያደራጀ ሲሆን ለባንኩ ደንበኞችም ባለ አራት ወለል የመኪና ማቆሚያ ማዘጋጀቱም ተገልጿል።
አርክቴክቸራል ዲዛይኑ በአገር  በቀሉ ኩባንያ  “እስክንድር አርክቴክት” ተሰርቶ ግንባታው በእውቁና በዓለም አቀፉ በየኮንስትራክሽን ዘርፍ ተጠቃሽ በሆነው “ቻይና ዢያንጉሹ” ኢንተርናሽናል ኩባንያ መከናወኑም ተገልጿል፡፡ የህብር ታወር የሚገኙ መሆኑም ታውቋል። መጀመር ባንኩ ከዚህ ቀደም ለዋና መስሪያ ቤትነትና ለሌሎች ሁለት ቅርንጫፎች ኪራይ ያወጣ  የነበረውን ከ1.5 ሚ ብር በላይ ወጪ እንደሚያስቀርለትና አሁን በአዲሱ ታወር ላይ በርካታ ክፍሎችን ለኪራይ ማዘጋጀቱን ጠቅሶ፤ ይህ ኪራይ ለሌሎች  ቅርንጫፎቹ የሚያወጣውን የኪራይ ወጪ እንደሚያካክስለት ነው ዋና ሥራ አስፈጻሚው የገለጹት፡፡
በህብር ታወር የምረቃ ሥነ ሥርአት ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ ባለ አክስዮኖች፣ የባንኩ ደንበኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙ መሆኑም ታውቋል።

Read 8429 times