Wednesday, 24 November 2021 00:00

በአለማችን የሲጋራ አጫሾች ቁጥር በመጠኑ ቅናሽ አሳይቷል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   የአለም የጤና ድርጅት በአለም ዙሪያ የሚገኙ ሲጋራ አጫሾች ቁጥር ከአምስት አመት በፊት ከነበረበት ጋር ሲነጻጸር በመጠኑ ቅናሽ ማሳየቱንና የአጫሾች ቁጥር በ2015 ከነበረበት 1.32 ቢሊዮን ዘንድሮ ወደ 1.30 ቢሊዮን ዝቅ ማለቱን አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ ሰሞኑን ባወጣው አለማቀፍ ሪፖርቱ እንዳለው፣ በ2020 የፈረንጆች አመት ከአጠቃላዩ የአለም ህዝብ 22.3 በመቶ ያህሉ ሲጋራ የሚያጨስ ሲሆን 38 ሚሊዮን ያህል የአለማችን ህጻናትና 231 ሚሊዮን ሴቶች አጫሽ ናቸው ተብሎ ይገመታል፡፡
የአጫሾች ቁጥር በመጪዎቹ አራት አመታት ውስጥ ወደ 1.27 ቢሊዮን ዝቅ ይላል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገለጸው ድርጅቱ፤ እ.ኤ.አ ከ2010 እስከ 2025 የሲጋራ አጫሽ ዜጎችን ቁጥር በ30 በመቶ ለመቀነስ ቃል ከገቡ የአለማችን አገራት መካከል ስድሳ ያህሉ ወደ ግባቸው እየተቃረቡ እንደሚገኙም ገልጧል፡፡ከአለማችን ዝቅተኛ የአጫሾች ቁጥር የተመዘገበው በአፍሪካ መሆኑንና ከአህጉሪቱ ህዝብ 10 በመቶው ሲጋራ ያጨሳል ተብሎ እንደሚገመት የጠቆመው ድርጅቱ፣ በአንጻሩ የደቡብና ምስራቅ እስያ አገራት ደግሞ ከፍተኛ የአጫሽ ቁጥር እንደተመዘገበባቸውና ከአገራቱ ህዝብ 29 በመቶው ወይም 432 ሚሊዮን ያህሉ አጫሽ መሆኑንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2907 times