Saturday, 09 October 2021 00:00

ሰምና ወርቅ የኪነ- ጥበብ ምሽት “ታሪክ ምን ይለናል” በሚል መርህ ሰኞ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት በየወሩ ሚካሄደው የኪነ- ጥበብ ምሽት ሰኞ ትቅምት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ከ11 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡
“ታሪክ ምን ይለናል” በሚል መርህ በሚካሄደው የኪ-ጥበብ ምሽት ላይ ወግ ግጥም ዲስኩርና ሙዚቃ ለታዳሚ የሚቀርብ ሲሆን፣በዕለቱም ሲሳይ መንግስቴ (ዶ/ር)፣ የህግ ባለሙያው ወንድሙ ኢብሳ፣ገዛኸኝ ፀጋው(ዶ/ር)፣አርክቴክት ዮሐንስ መኮንን፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ግሩም ተበጀ፣ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም፣ ጋዜጠኛ የኑስ መሃመድ፣ ገጣሚያኑ መንበረማሪያም ሀይሉ፣ መዝገበቃል አየለ ገላጋይ፣ ሀይማኖት አሰፋና ምንሊክ ብርሃኑ ከአድዋ ባንድ ጋር በመሆን ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡ በዶ/ር ሙሉ የጥርስ ህክምና ስፖንሰር የተደረገው በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመታደም የመግቢያ ዋጋው 100 ብር ሲሆን የመግቢያ ቲኬቶቹ በጃዕፋር፣ በዮናስ በዘወዱ መፃህፍት መደብሮች እንደሚገኙም ታውቋል፡፡


Read 6693 times