ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በአለማቀፍ ደረጃ ተወዳጅነትን ያፈራው ቻይና ሰራሹ የአጫጭር ቪዲዮዎች ማሰራጫ ድረገጽ ቲክቶክ ወርሃዊ ቋሚ ደንበኞች ቁጥር ከ1 ቢሊዮን ማለፉን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የቻይናው ባይትዳንስ ኩባንያ ንብረት የሆነው ቲክቶክ በመላው አለም ከፍተኛ ተወዳጅነት ካገኘባቸው አገራት መካከል አሜሪካ፣ አውሮፓ፣ ብራዚልና የደቡብ ምስራቅ እስያ አገራት እንደሚገኙበት የጠቆመው ዘገባው፤ ቲክቶክ ምንም እንኳን በአሜሪካና በአንዳንድ አገራት የተለያዩ የገደብ ውሳኔዎች ቢተላለፉበትም፣ የተጠቃሚዎቹ ቁጥር ግን በከፍተኛ ሁኔታ በማደግ ላይ እንደሚገኝ ገልጧል፡፡
በአለማቀፍ ደረጃ የቲክቶክ ተጠቃሚዎች ቁጥር እስካለፈው 2020 ሃምሌ ወር 689 መድረሱን ያስታወሰው ዘገባው፤ አፕሊኬሽኑ እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ከ2 ቢሊዮን ጊዜያት በላይ ዳውንሎድ መደረጉንም አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ