Print this page
Saturday, 11 September 2021 00:00

ከሙኒክ ባሻገር ትርጉም መፀፅሐፍ ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በደራሲና ጋዜጠኛ ሲሞን ሪቭ `one day in septmeber` በሚል ርዕስና በእውቁ ተርጓሚና ደራሲ ጥላሁን ግርማ አንጎ “ከሙኒክ ባሻገር” በሚል ወደ አማርኛ የተመለሰው አዲስ መፅሀፍ ገበያ ላይ ዋለ። መጽሐፉ በዋናነት በ1972 በሙኒክ ኦሎምፒክ  በጥቁሩ መስከረም” የአሸባሪው ቡድን የተፈፀመውን ግድያና የእስራኤል የበቀል ዘመቻ የሆነውን “መቅሰፍተ-ኤል” ሙሉ ታሪክ ሰንዶ የያዘ ስለመሆኑ ተርጓሚው ገልጿል፡፡
መፅሀፉ መነሻውን በሙኒክ ኦሎምፒክ የተፈፀመውን ግድያና ሽብር ያድርግ እንጂ አጠቃላይ የሽብርተኝነን አስከፊነት፣ በሽብር ጥቃት ሰለባ የሆኑ ሰዎች ስቃይ፣ የቤተሰቦቻቸውን በሀዘን መሰበርና አጠቃላይ ህመሙን ያስቃኛል ተብሏል። በ493 ገፅ የተቀነበበው መፅሐፉ በ350 ብርና በ40 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡
ደራሲና ተርጓሚ ጥላሁን ግርማ አንጎ ከዚህ  ቀደም የእውቁን ደቡብ አፍሪካዊ ኮሜዲያን ትሬቨርነዋህን ታሪክ የሚያስቃኘውን `born a crime` መፅሐፍ “የአመጻ ልጅ” በሚል ከመተርጎሙም ባሻገር 13 ደራሲያን በተሳተፉበት “አቦል” መጽሐፍ  ላይ “የምርቃቱ መጽሄት” የተሰኘ አጭር ልቦለድና “በካልካታ ጎዳና” የተሰኘ አጭር ትርጉም ለንባብ ማብቃቱ አይዘነጋም  

Read 19609 times
Administrator

Latest from Administrator