Print this page
Saturday, 11 September 2021 00:00

የአዲስ ዓመት ምኞት

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ያሳለፍነው  ዓመት  በጎና ክፉ ገፅታን ያስተናገድንበት ዘመን ነበር። ከበጎ ገፅታው ብንጀምር ከ3 ዓመት በፊት የተጀመረው የለውጥ ሂደት የቀጠለበት፣ በርካታ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ የቻልንበት፣ በብዙ ፈተናዎችና መሰናክሎች ውስጥ ሆነን የሕዳሴ ግድብን ሁለተኛ ዙር ሙሌት ለማጠናቀቅ የቻልንበት፣- 6ኛውን አገር አቀፍ ምርጫ በስኬት ያከናወንበት በጎ ዘመን ነበር።
ከዚህ ጎን ለጎን የኢትዮጵያን ዕድገትና ህልውና በማይፈልጉ አገራት የሚደረጉ ከፍተኛ ጫናን ያስተናገድንበት፣ የሱዳን፣ ጦር ወደ አገራችን በእብሪት ዘልቆ የገባበት፣ መንግስት በታላቅ ትዕግስት ሁኔታውን እየተከታተለ ያለበት፣ አገራችን በውስጥና በውጭ ሊያጠፏት ካሴሩ ወገኖች ጋር ወደ ጦርነት እንድትገባ የተገደደችበት፣ በዚህም በርካታ ወገኖቻችንን ያጣንበት፣ ስደትና መፈናቀል  የበዛበት… ከባድ ጊዜ ነበር 2013 ዓ.ም። በአጠቃላይ ዘመኑ ዕድሎች ፈተናዎችና ስኬቶች ያስተናገደ  ነበር።
መጪው አዲስ ዘመን አገራችን ሰላሟን የምታገኝበት፣ ግጭቱና ጦርነቱ እልባ የሚያገኝበት፣ አዲሱ መንግስት ግጭቶችን በዘላቂነት ለማስወገድ የሚችልበትን መንገድ የሚፈልግበት፣ ሁለቱ ተርባይኖች ኃይል በማመንጨት መብራት ማፍለቅ የሚጀምሩበት፣ ለሁለገብ ብልፅግናችን በጋራ የምንቆምበት ዘመን እንዲሆንልን እመኛለሁ።
ዶ/ር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ
የውሃና መስኖ ሚኒስትር
ዓመቱን በብዙ ችግሮችና ፈተናዎች አልፈን ዛሬ ላይ ደርሰናል። መጪው አዲስ ዓመት ለአገራችን መልካም ነገሮች የሚሆንበት፣ አገራችን ሰላም ሆና ህዝቦቿ በሰላም ወጥተው የሚገቡባት፣ ዕቅዳችንን የምናሳካበት፣ ዘመን እንዲሆን ምኞቴ ነው። አገራችን ኢትዮጵያ ወደ ተረጋጋ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የምትገባበት፣ ህዝቦቿ ተረጋግተው በልማቱ ላይ ትኩረት የሚያደርጉበት ጊዜ እንዲሆንም እመኛለሁ።
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ፤


Read 10024 times
Administrator

Latest from Administrator