Print this page
Sunday, 29 August 2021 00:00

በአለማችን ከ5 ቢ. በላይ የኮሮና ክትባቶች ቢሰጡም፣ በ3 አገራት ክትባት አልተጀመረም

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በመላው አለም እስከያዝነው ሳምንት አጋማሽ ድረስ ከ5 ቢሊዮን በላይ የኮሮና ክትባቶች ለተጠቃሚዎች መሰጠታቸው ቢዘገብም፣ ብሩንዲ፣ ኤርትራና ሰሜን ኮርያ ገና አሁንም ድረስ የክትባት መርሃግብር አለመጀመራቸው ተነግሯል፡፡
እስካሁን በአለማቀፍ ደረጃ ከተዳረሰው 5 ቢሊዮን በላይ የኮሮና ክትባት ውስጥ ወደ ግማሽ የሚቃረበው ወይም 1.96 ቢሊዮን ያህሉ በቻይና መሰጠቱን የዘገበው አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ፣ ህንድ 589 ሚሊዮን፣ አሜሪካ ደግሞ 363 ሚሊዮን የኮሮና ክትባቶች የተሰጡባቸው ተከታዮቹ የአለማችን አገራት መሆናቸውንም አመልክቷል፡፡
ካላቸው አጠቃላይ የህዝብ ቁጥር አንጻር ብዛት ያላቸውን ሰዎች በመከተብ ደግሞ፣ ከአለማችን አገራት መካከል የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ኡራጓይና እስራኤል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ መያዛቸውን አመልክቷል፡፡


Read 2628 times
Administrator

Latest from Administrator