Print this page
Saturday, 28 August 2021 14:16

ቻይናውያኑ የቶክዮ ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያዎቻችን ተላላጡብን ሲሉ ከሰሱ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    በቅርቡ በተካሄደው የ2020 የቶክዮ ኦሎምፒክ ቻይናን ወክለው በመወዳደር ያሸነፉ 2 አትሌቶች የተሸለምናቸው የወርቅ ሜዳልያዎቻችን ገና አንድ ወር እንኳን ሳይሞላቸው መላላጥ ጀምረዋል ሲሉ በአዘጋጅ ኮሚቴው ላይ ክስ መመስረታቸው ተነግሯል፡፡
ክሱን በማህበራዊ ድረገጽ ባስተላለፉት መልዕክት ያደረሱት በውሃ ዋና እና በጂምናስቲክ አገራቸውን ወክለው በተሳተፉበት ኦሎምፒክ አሸንፈው የወርቅ ሜዳሊያ የተሸለሙ ቻይናውያን መሆናቸውን የዘገበው ግሎባል ታይምስ ድረገጽ፣ የኦሎምፒክ አዘጋጅ ኮሚቴው ተወካዮች በበኩላቸው ምናልባት መላላጡ የተፈጠረው ሜዳሊያዎቹን ለመጠበቅ ታስቦ በተቀባው ነገር ሳቢያ ሊሆን ይችላል ሲሉ ማስተባበላቸውን ገልጧል፡፡
አትሌቶቹ በሜዳሊያዎቹ ጥራትና ትክክለኛነት ላይ ጥርጣሬ ካደረባቸው አስፈላጊውን አቤቱታ ለሚመለከተው አካል በማቅረብና ተገቢውን ክፍያ በመፈጸም ተተኪ ሜዳሊያ ማግኘት እንደሚችሉ ኮሚቴው መግለጹንም ዘገባው አክሎ አስነብቧል፡፡

Read 1772 times
Administrator

Latest from Administrator