Print this page
Monday, 23 August 2021 00:00

የኮሮና ክትባት አጭበርባሪዎች በዝተዋል ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

3 የኮሮና መድሃኒቶች በምርምር ሂደት ላይ ይገኛሉ

            የተለያዩ አይነት የኮሮና ቫይረስ ክትባቶችን በቅናሽ ዋጋ እናቀርባለን እያሉ መንግስታትን ጭምር የሚያጭበረብሩ ቡድኖች መበራከታቸውን አለማቀፉ የፖሊስ ጥምረት ኢንተርፖል ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ ማስጠንቀቁን ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
መሰል አጭበርባሪዎች 40 በሚደርሱ የተለያዩ የአለማችን አገራት ላይ የኮሮና ክትባት ሽያጭ ጥቃቶችን ማድረሳቸውን የስታወቀው ኢንተርፖል፣ ቡድኖቹ በተደራጀ እና በተጠና ሁኔታ ስለሚንቀሳቀሱ መንግስታት ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ቡድኖቹ ከክትባት አምራች ኩባንያዎች ጋር ህጋዊ የስራ ግንኙነትና ውክልና ያላቸው በማስመሰል በሃሰተኛ የኤሜይልና የስልክ መልዕክቶች አገራትን ለግዢ እንደሚያግባቡ የጠቆመው ዘገባው፣ ፈቃድ ያላገኙ ወይም በገበያ ላይ የሌሉ ክትባቶችን ጭምር ለመሸጥ እንደሚስማሙና ከፍተኛ ኪሳራ እንደሚያደርሱ መነገሩንም ገልጧል፡፡
በሌላ የኮሮና ቫይረስ ዜና ደግሞ፣ የአለም የጤና ድርጅት ሶስት አዳዲስ የኮሮና ቫይረስ መድሃኒቶች በምርምር ሙከራ ላይ እንደሚገኙ ከሰሞኑ ያስታወቀ ሲሆን፣ አርቴሱኔት፣ ኢሜቲኒብና ኢንፊሊክሲማብ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው መድሃኒቶቹ በቀጣይ በ52 የተለያዩ የአለማችን አገራት የኮሮና ተጠቂዎች ላይ እንደሚሞከሩና ውጤታማ ሆነው ከተገኙ ጥቅም ላይ የሚውሉበትን ፈቃድ እንደሚያገኙም አመልክቷል፡፡


Read 2376 times
Administrator

Latest from Administrator