Print this page
Tuesday, 03 August 2021 00:00

ቶክዮ በግንባታ ዋጋ ውድነት ከአለም ከተሞች 1ኛ ናት ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 አንድ አለማቀፍ የገበያ ጥናት ተቋም ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው አመታዊ የግንባታ ገበያ አለማቀፍ ሪፖርት መሰረት፣ የጃፓን ርዕሰ መዲና ቶክዮ ከአለማችን ከተሞች መካከል በኮንስትራክሽን ዘርፍ የዋጋ ውድነት በ1ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ፎርብስ መጽሄት ዘግቧል፡፡
ተርነር ኤንድ ታውንሴንድ በ45 የአለማችን አገራት በሚገኙ ከተሞች 90 ገበያዎች ላይ ያደረገውን የኮንስትራክሽን ገበያ ጥናት መሰረት በማድረግ ከሰሞኑ ይፋ ያደረገውን የ2021 የፈረንጆች አመት አለማቀፍ የኮንስትራክሽን ዋጋ ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ በቶክዮ አንድ ስኩየር ሜትር ስፋት ያለው ግንባታ ለማከናወን በአማካይ 4,002 የአሜሪካ ዶላር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን ይህም በአለማችን ከፍተኛው ዋጋ ነው፡፡
ለአንድ ስኩየር ሜትር ግንባታ 3,894 በዶላር ወጪ የሚደረግባት ሆንግ ኮንግ በአመቱ የተቋሙ የኮንስትራክሽን ዋጋ ውድነት ዝርዝር በሁለተኛ ደረጃ ላይ ስትቀመጥ፣ የአሜሪካዋ ሳን ፍራንሲስኮ በ3,720 ዶላር ሶስተኛ ሆናለች፡፡
የአሜሪካዋ ከተማ ኒው ዮርክ ሲቲ በ3511 ዶላር፣ የስዊዘርላንዶቹ ከተሞች ጄኔቫና ዙሪክ በ3478 ዶላርና በ3375 ዶላር፣ የአሜሪካዎቹ ቦስተንና ሎስ አንጀለስ በ3203 እና በ3186 ዶላር አማካይ የአንድ ስኩየር ሜትር ግንባታ ዋጋ ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ የያዙ የአለማችን ከተሞች መሆናቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡


Read 2578 times
Administrator

Latest from Administrator