Print this page
Saturday, 31 July 2021 00:00

አፕል በ3 ወራት 81 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በሩብ አመቱ 40 ቢሊዮን አይፎን ስልኮችን ሸጧል

               በአለማችን እጅግ ከፍተኛ የገበያ ዋጋ ያለው ቁጥር አንድ ኩባንያ የሆነው የአሜሪካው የቴክኖሎጂ ኩባንያ አፕል እስከ ሰኔ በነበሩት ያለፉት 3 ወራት በድምሩ 81 ቢሊዮን ዶላር ያህል አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱንና ይህም፣ በኩባንያው ታሪክ ከፍተኛ ሆኖ የተመዘገበ የሁለተኛ ሩብ አመት ገቢ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ዋና መስሪያ ቤቱን በካሊፎርኒያ ያደረገው ግዙፉ ኩባንያ አፕል በሩብ አመቱ ያገኘው ገቢ ካለፈው አመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር በ35 በመቶ ያህል ብልጫ እንዳለው የጠቆመው ዘገባው፣ በሩብ አመቱ ያገኘው የተጣራ ገቢ በበኩሉ 21.7 ቢሊዮን ዶላር መሆኑን ኩባንያው በሳምንቱ መጀመሪያ ይፋ ያደረገውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው አመልክቷል፡፡
ኩባንያው በሩብ አመቱ ከፍተኛ ገቢ እንዲያገኝ ካስቻሉት ምክንያቶች መካከል የአይፎን ሞባይል ስልኮቹ ሽያጭ ማደጉ በቀዳሚነት እንደሚጠቀስ የጠቆመው ዘገባው፣ ከአጠቃላይ ገቢው 53 በመቶ ያህሉ ከዚሁ ሽያጭ መገኘቱንና ኩባንያው ባለፉት 3 ወራት ብቻ 40 ቢሊዮን ያህል አይፎኖችን መሸጡንም ገልጧል፡፡
የአፕል የአክሲዮን ዋጋ ባለፉት አምስት አመታት በ500 በመቶ ያህል ማደጉን ያስታወሰው ዘገባው፣ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው አጠቃላይ ሃብትና የገበያ ዋጋ ወደ 2.5 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱንም አክሎ ገልጧል፡፡


Read 1152 times
Administrator

Latest from Administrator