የዘንድሮ የአፍሪካ ሕፃናት ቀንና “የአንድሮ ሜዳ ቁጥር 2” መፅሐፍ ምረቃ ነገ በባህርዳር አቫንገር ብሎ ናይል ሆቴል እንደሚካሄድ አዘጋጁ ሰምና ወርቅ ሚዲያና ፕሮሞሽን አስታወቀ።
በዕለቱ ጥናታዊ የምርምር ስራ በመጋቤ ሀዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰና ዶ/ር ጌትነት ፈለቀ የሚቀርብ ሲሆን በአዲስ አበባና በባህርዳር ያሉ ተመራማሪ የአንድሮ ሜዳ ህጻናት ይሳተፋሉም ተብሏል፡፡ በዚሁ ሥነ-ስርዓት ላይ “አንድሮሜዳ ቁጥር ሁለት” እና “የወርቅ ዘንግ” መፃህፍት የሚመረቁ ሲሆን በእውቅ ገጣሚያን ግጥም፣ በኢትዮጵያ የባህል ቡድን ምርጥ ኪነ- ጥበባዊ ዝግጅቶች፣ በስነ-ፈለክ መመልከቻ የሰማይ ምልከታ ሥነ-ስርዓት እንደሚከናወን የጠቆመው አዘጋጁ፣ በፕሮግራሙ ላይ ታዋቂ ግለሰቦች እንደሚታደሙ ተገልጿል፡፡
Saturday, 24 July 2021 00:00
የአፍሪካ ህጻናት ቀንና “የአንድሮሜዳ ቁጥር ሁለት” መፅሐፍ ምረቃ ነገ በባህርዳር ይካሄዳል
Written by Administrator
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና