Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 01 September 2012 11:58

“ጉማ የፊልም ሽልማት” ሊቀርብ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢትዮ ፊልም ፒ.ኤል.ሲ እና ኢ ቢ ኤስ ቴሌቭዢን በመተባበር የሚያዘጋጁት “ጉማ የፊልም ሽልማት” በታህሣሥ ወር ሊቀርብ ነው፡፡ አዘጋጆቹ ባለፈው ሰኞ ቦሌ መድሃኒዓለም አካባቢ በሚገኘው ሐርመኒ ሆቴል በሰጡት መግለጫ በ16 ዘርፎች ለመሸለም መዘጋጀታቸውንና ዝግጅቱ እንደተለመደው በአውደርእይ መልክ እንደማይሆን ተናግረዋል፡፡ ፈርቀዳጅ ከሆነው የኢትዮጵያ የመጀመሪያ ባለቀለም ፊልም ስያሜውን ያገኘው “ጐማ የፊልም ሽልማት” ለዚሁም የፊልሙን አዘጋጅ አንጋፋው የፊልም ባለሙያ ሚሼል ፓፓታኪስን ማነጋገራቸውን አዘጋጆቹ ተናግረዋል፡፡

የፊልም ሽልማቱን ለማዘጋጀት የሰባት ወራት ጥናት ማካሄዳቸውን የገለፁት የኢትዮ ፊልምስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ብርሃነ መዋ፤ የሽልማቱ ወጪ በሙሉ በድርጅታቸው እንደሚሸፈንና ባለፊልሞች ውድድር እንዲያሸንፉ ብቻ ሳይሆን የተሻለ ሥራ ይዘው ለሕብረተሰቡ እንዲቀርቡ ነው ጥረታችን ብሏል፡፡ የኢቢ ኤስ ቴሌቪዢን ጀነራል ማናጀር አቶ አማን ፍስሃ ጽዮን፤ ጣቢያቸው በፊልም ላይ የተሻለ ሽፋን እንደሚሰጥና ከኢትዮ ፊልምስ ጋር ተባብረው በመስራት ላይ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ሀገር አቀፍ ፊልሞችን ብቻ የሚያስተናግደው የፊልም ሽልማት ምዝገባ በድረገጽ የተጀመረ ሲሆን ሽልማቱ ለአምስት ተከታታይ ዓመታት እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አዘጋጆቹ የአሸናፊ ፊልም ምርጫ ሂደትን ሲገልፁ፤ አንድ ሰው ከአንድ በመቶ በታች የሆነ ድምጽ ስለሚኖረው ሚዛናዊነቱ እንደሚጐላ ያላቸውን እምነት ተናግረዋል፡፡

 

Read 1386 times