Sunday, 27 June 2021 16:52

በአመቱ 8 ሺህ 500 የአለማችን ህጻናት ለውትድርና ተዳርገዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ባለፈው የፈረንጆች አመት 2020 በተለያዩ የአለማችን አገራት በተቀሰቀሱ ግጭቶችና ጦርነቶች ከ8ሺህ 500 በላይ ህጻናት በወታደርነት እንዲያገለግሉ መደረጉን የገለጸው ተመድ፤ ተጨማሪ 2ሺህ 700 ያህል ህጻናት መገደላቸውንና ሌሎች 5ሺህ 748 ያህል ህጻናት ደግሞ መቁሰላቸውን አስታውቋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስ ባለፈው ሰኞ ለጸጥታው ምክር ቤት ያቀረቡትን ሪፖርት ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፤ በአመቱ በተለያዩ የአለማችን አካባቢዎች በተቀሰቀሱ 21 ግጭቶች በ19 ሺህ 379 ህጻናት ላይ ግድያ፣ ወሲባዊ ጥቃትና ጠለፋን ጨምሮ የተለያዩ አይነት ጥቃቶችና በደሎች መፈጸማቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
በመላው አለም በአመቱ በተቀሰቀሱ ግጭቶች እጅግ ከፍተኛ ጥቃቶችና በደሎች የተፈጸሙባቸው አገራት ሶማሊያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ አፍጋኒስታን፣ ሶርያና የመን መሆናቸውንም ዋና ጸሃፊው ባቀረቡት ሪፖርት አመልክተዋል፡፡

Read 3131 times