Saturday, 19 June 2021 16:57

የምርጫው ወሳኝ መረጃዎች ምን ይላሉ?

Written by 
Rate this item
(4 votes)

  1. የተወዳዳሪዎች ብዛት
በኦሮሚያ ክልል፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ በአብዛኞቹ ቦታዎች፣ አይወዳደሩም፡፡
ገዢው ፓርቲ፣ በኦሮሚያ 60% ገደማና ከዚያ በላይ፣ ያለተወዳዳሪ ነው የቀረበው፡፡
2.  የብርቱ ፉክክር አካባቢዎች
አዲስ አበባ፣ ለከተማ ምክር ቤትና ለፓርላማ፣ ሶስት ፓርቲዎች በብርቱ የሚፎካከሩበት ሆኗል፡፡ ብልፅግና፣ ኢዜማና ባልደራስ፡፡
የአማራ እና የደቡብ ክልሎች፣ በተለይ ከተሞችና ዙሪያቸው፣ የበርካታ ፓርቲዎች፣ ዋና የፉክክር አካባቢዎች ናቸው፡
3. የምርጫው መንፈስ
የአምስት ዓመት የአመፅ፣ የለውጥና የነውጥ ክስተቶችን ተከትሎ የሚካሄደው ምርጫ፣ ደብዘዝና ረጋ ያለ ስሜት ተላብሷል፡፡
በተጠበቀው ብዛት፣ መራጭ፣ በጊዜ አልተመዘገበም፡፡ ግማሽ ያህል ሳይመዘገብ፤ የጊዜ ገደቡ በመድረሱ ነው፣ የተራዘመው፡፡
የኮቪድ ወረርሽኝ፣ የሰላም መደፍረስ፣ የፀጥታ ችግር፣ ግጭትና ጥቃት፣ የምርጫውን መንፈስ አደብዝዘውታል፡፡
በርካታ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመረጋጋት አዝማሚያ መያዛቸው፣ ገዢው ፓርቲም የበርካታ ሚሊዮን አባላት መዋቅሩን በሙሉ ሃይል አለማዝመቱ፣ የምርጫ ትኩሳትን የሚያበርድ ሆኗል፡፡
የምርጫውንና የውጤቱን አዝማሚያ በቅጡ ለመለካት፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በቂ የሙያና የብስለት አቅም ገና አልተፈጠረም፡፡
የምርጫ መረጃዎችን ማደራጀትና የጥናት ዳሰሳዎች፣ ማካሄድ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ፣ ገና በወጉ አልተጀመሩም፡፡ ሰፊ ጥናትና ጥልቅ ትንተና ይቅርና፣ በጥሬው የዜጎች አስተያየትን ወይም የመራጮችን ዝንባሌ፣ የማጠያየቅ ልማድም የለም፡፡
የብዙ መራጮችን ትኩረት የሚስብ፣ ብዙ ዜጎችን የሚያሳስብ ጉዳይ ምን ምን እንደሆነ፣ ከፓርቲዎችና ከፖለቲከኞች አቋም ጋር በማዛመድ የምርጫውን አዝማሚያ የሚጠቁም፣ የተጨበጠ መረጃና የተሟላ ትንታኔ ማቅረብ፣ ከኢትዮጵያ አቅም በላይ ነው፡፡
    እንዲያም ሆኖ፣ የተወዳዳሪዎች ብዛት፣ የፓርቲዎች አቅም፣ የመራጮች ምዝገባ፣ ጠቅላላ የምርጫው መንፈስና የአገሪቱ ሁኔታ፣ የማመዛዘኛ መስፈርቶች ናቸው፡፡    የተወዳዳሪዎች ቁጥር ማነስ፣ ለገዢው ፓርቲ አመቺ፣ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ጉዳት ነው፡፡ የተወዳዳሪዎች ብዛት ደግሞ፣ የገዢውን ፓርቲ ፈተና፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን አቅም ይጠቁማል፡፡ ነገር ግን፣ በርካታ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እርስ በርሳቸውም ተፎካካሪ ስለሆኑ፣ የመራጮችን ድምጽ የሚከፋፍልና የሚበትን፣ በዚህም የገዢውን ፓርቲ ፈተና የሚያቀል ሊሆን ይችላል፡፡ በኦሮሚያ ክልል፡
ለ171 የፓርላማ ወንበር የተመዘገበው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ 268 ተወዳዳሪዎች ይፎካከራሉ፡፡
በ104 የፓርላማ ወንበሮች ላይ፣ ብልፅግና ፓርቲ ብቻ ነው ተወዳዳሪ ያስመዘገበው፡፡
በአማራ ክልልም፡
ለ128 የፓርላማ ወንበሮች፣ በአጠቃላይ ከ740 በላይ ተወዳዳሪዎች ይፎካከራሉ፡፡ ለእያንዳንዱ ወንበር፣ በአብዛኛው 5 እና ከዚያ በላይ ተወዳዳሪዎች አሉ፡፡ ብዙ ፓርቲዎች የተረባረቡበት የአዲስ አበባ ብርቱ ፍክክር!
በአዲስ አበባ፣ ለእያንዳንዳንዱ የፓርላማ ወንበር፣ 7 ወይም ከዚያ በላይ ፓርቲዎች ይፎካከራሉ፡፡
በአዲስ አባባ፣ ለ23 የፓርላማ ወንበር በሚፎካከሩ ፓርቲዎች የቀረቡ እጩዎች፣


Read 13713 times