Wednesday, 09 June 2021 00:00

የ1.79 ሚ. ዶላሩ የአለማችን ውድ መድሃኒት ለ5 ወሩ ጨቅላ ሊሰጥ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በአከርካሪ አጥንት ህመም ሲሰቃይ የቆየው እንግሊዛዊ የ5 ወር ጨቅላ በአለማችን በዋጋው ውድነት አቻ እንደማይገኝለት የተነገረውንና ዞጌንስማ የተባለውን በ1.79 ሚሊዮን ፓውንድ የሚሸጥ መድሃኒት በመውሰድ የመጀመሪያው ታካሚ ሊሆን መዘጋጀቱን ስካይ ኒውስ ዘግቧል፡፡
አርተር ሞርጋን የተባለውና በለንደኑ ኤቪሊና የህጻናት ሆስፒታል ክትትል እየተደረገለት የሚገኘው ይህ ጨቅላ፣ ከዘረመል ጋር ተያይዘው የሚመጡ በሽታዎችን በመፈወስና ከሞት በመታደግ ረገድ ውጤታማ ነው የተባለውን ይህን አሜሪካ ሰራሽ መድሃኒት ለመውሰድ መዘጋጀቱን ነው ዘገባው ያመለከተው፡፡
ጨቅላው ይህንን ውድ መድሃኒት የመውሰድ ዕድል ያገኘው፣ የእንግሊዝ የማህበረሰብ የጤና ተቋም ባደረገለት የገንዘብ ድጋፍ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ እዚህ ግባ የሚባል ገቢ የሌለው የጨቅላው አባት ልጁን ከሞት ለመታደግ የሚያስችለውን ይህንን ውድ መድሃኒት ለመግዛት አቅም እንደሌለው ስለሚያውቅ በከፍተኛ ሁኔታ ተጨንቆ እንደነበር፣ በተደረገለት ድጋፍም መደሰቱንና ልጄ ይተርፋል ብሎ ተስፋ እንደሚያደርግ መናገሩን አመልክቷል፡፡

Read 1397 times