Tuesday, 08 June 2021 00:00

ዩቲዩብ በአመቱ ለሙዚቃ 4 ቢ. ዶላር መክፈሉን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    ታዋቂው የቪዲዮ ማሰራጫ ድረገጽ ዩቲዩብ ባለፉት 12 ወራት ብቻ ከሙዚቃው ኢንዱስትሪ ጋር በተያያዘ ከ4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ክፍያ መፈጸሙን ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
በአልፋቤት ኩባንያ ስር የሚገኘው ዩቲዩብ በ2020 የፈረንጆች አመት፣ ከማስታወቂያ 19.78 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን ከሰሞኑ ያስታወቀ ሲሆን፣ ከዚህም ውስጥ 20 በመቶ ያህሉን ወይም ከ4 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚሆነውን የተለያዩ ሙዚቃዎችን ላስተላለፈላቸው ሙዚቀኞች፣ የሙዚቃ ደራሲዎች፣ የሙዚቃ ፈጠራ መብት ባለቤቶችና በኢንዱስትሪው ውስጥ ለሚገኙ አካላት መክፈሉን ገልጧል፡፡
በሙዚቃ ስራዎቻቸው ክፍያ የሚፈጽምላቸው ደንበኞቹ ቁጥር በ2021 የመጀመሪያው ሩብ አመት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ያስታወቀው ዩቲዩብ፤ እ.ኤ.አ ከ2019 አንስቶ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ በድምሩ 3 ቢሊዮን ዶላር ያህል መክፈሉንም አስታውሷል፡፡

Read 2659 times