Print this page
Thursday, 20 May 2021 00:00

የህንዱ ኮሮና ቫይረስ ዝርያ ከ50 በላይ አገራት ተዛምቷል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 በብዛት ከከተቡ አገራት በ80 በመቶው ኮሮና ብሶባቸዋል

           የአለም የጤና ድርጅት “በአለማቀፍ ደረጃ ልዩ ስጋት ፈጥሯል” ብሎ የፈረጀውና ከሌሎች የኮሮና ቫይረስ ዝርያዎች ሁሉ በቀላሉ የመሰራጨት አቅም ያለው በህንድ የተገኘው “B.1.617’’ የተባለ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ወደ 50 የአለማችን አገራት መዛመቱንና ከእነዚህም መካከል ሰባቱ የአፍሪካ አገራት መሆናቸውን ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡
የአለም የጤና ድርጅት ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ይህ የቫይረሱ ዝርያ ከህንድ ውጭ በርካታ ሰዎችን ካጠቃባቸው አገራት መካከል እንግሊዝ በቀዳሚነት የምትጠቀስ ሲሆን፣ ቫይረሱ ብራዚልንና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ ወደ 50 ያህል አገራት መዛመቱን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡
ከዚህ ቀደም ቫይረሱ የተገኘባቸው የአፍሪካ አገራት ኬንያ፣ ሞሮኮ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ኡጋንዳ መሆናቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ከሰሞኑ ደግሞ ወደ አልጀሪያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎና ናይጀሪያ መግባቱ መረጋገጡንም አክሎ ገልጧል፡፡ ኦል አፍሪካን ኒውስ በበኩሉ፣ በአፍሪካ አህጉር እስካሁን ድረስ ከ14 ሚሊዮን በላይ የኮሮና ቫይረስ ክትባቶች መሰጠታቸውን ከሰሞኑ ባወጣው ዘገባ አስነብቧል፡፡
በሌላ የኮሮና ቫይረስ ዜና ደግሞ፣ በመላው አለም ለበርካታ ዜጎቻው የኮሮና ክትባትን በስፋት ካዳረሱ ቀዳሚዎቹ አገራት መካከል 80 በመቶ ያህሉ ከህዝብ ብዛት አንጽር የቫይረሱ ስርጭት ከወትሮው ብሶ መቀጠሉ ተዘግቧል፡፡
በአለማችን የኮሮና ክትባትን በስፋት ከሰጡት ቀዳሚዎቹ አገራት ሲሼልስ፣ እስራኤል፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ቺሊ እና ባህሬን መካከል ከእስራኤል በቀር ሁሉም የቫይረሱ ስርጭት ከወትሮው በከፋ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ መረጋገጡንና ይህም በክትባቶቹ ፍቱንነት ላይ ጥያቄ ማስነሳት መጀመሩን ፎርብስ ዘግቧል፡፡






Read 4770 times
Administrator

Latest from Administrator