Wednesday, 19 May 2021 00:00

የኡጋንዳው ሙሴቬኒ ለ6ኛ ዙር የስልጣን ዘመን ቃለ መሃላ ፈጽመዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  ሳልቫ ኬር የደቡብ ሱዳንን ፓርላማ በተኑ

          ኡጋንዳን ላለፉት 35 ያህል አመታት ያስተዳደሩትና ባለፈው ጥር ወር በተካሄደ አወዛጋቢና ደም አፋሳሽ ምርጫ ያሸነፉት ፕሬዚዳንት ዮሪ ሙሴቬኒ ባለፈው ረቡዕ ለ6ኛ ዙር የስልጣን ዘመን ቃለ መሃላ መፈጸማቸው ተነግሯል፡፡
የ76 አመቱ ሙሴቬኒ ለቀጣዮቹ ስድስት አመታት አገሪቱን ለማስተዳደር በመዲናይቱ ካምፓላ በይፋ ቃለ መሃላ በፈጸሙበት በዓለ ሲመት ላይ ከ10 በላይ የአፍሪካ አገራት መሪዎች የተገኙ ሲሆን፣ ሰኞ ዕለት የአገሪቱ ፖሊስ በዓለ ሲመቱን ለማወክ አቅደዋል ያላቸውን ከ40 በላይ ተጠርጣሪዎች ማሰሩን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በሌላ የአፍሪካ ዜና ደግሞ፣ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር በአገሪቱ ከሶስት አመታት በተደረሰው የሰላም ስምምነት የተገቡ ቃሎችን ተፈጻሚ ለማድረግ በሚል ባለፈው ቅዳሜ የአገሪቱን ፓርላማ መበተናቸውን ኦልአፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱን የፓርላማ አባላትንና ከፍተኛ ባለስልጣናት ከገዥው ፓርቲ ብቻ ሳይሆን ከተቀናቃኝ ፓርቲዎች ለመምረጥ ታስቦ በ2018 የተፈጸመው ስምምነት 25 በመቶ የፓርላማ አባላትን ከተቀናቃኙ የሬክ ማቻር ፓርቲ ለማድረግ ተወስኖ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ በዚህ መሰረትም ሳልቫ ኬር ፓርላማውን መበተናቸውንና አዲሱን ፓርላማ ከሰሞኑ ያዋቅራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክቷል፡፡


Read 2436 times