Print this page
Tuesday, 27 April 2021 00:00

ኮሮናን በወራት ውስጥ መቆጣጠር የሚቻልበት መላ መገኘቱ ተነገረ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   አለማችን ከአንድ አመት በላይ አሳር መከራዋን ሲያሳያት የከረመውንና አሁንም በእጅግ ከፍተኛ ፍጥነት በመሰራጨት ላይ የሚገኘውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በወራት ጊዜ በቁጥጥር ስር ማዋል እንደምትችል የገለጸው የአለም የጤና ድርጅት፤ ይህን ማድረግ የሚቻለው ግን አስፈላጊ ሃብቶችን በፍትሃዊነት መከፋፈል ሲቻል ብቻ እንደሆነ አመልክቷል፡፡
የድርጅቱ ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም በሳምንቱ መጀመሪያ በሰጡት መግለጫ፤ ኮሮናን በቀጣዮቹ ወራት በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚያስችሉ መሳሪያዎች ቢገኙም የአለማችን አገራት እነዚህን መሳሪያዎች በፍትሃዊነት መከፋፈልና በዘላቂነት መጠቀም ካልቻሉ ግን ቫይረሱን በቁጥጥር ስር ማዋል አይቻልም ማለታቸውን የዘገበው ሮይተርስ፤ የተገኘው መላ ምን እንደሆነ ግን በግልጽ አልተናገሩም ብሏል፡፡
ቫይረሱ አሁንም በመላው አለም በእጅግ ከፍተኛ ፍጥነት በመሰራጨት ላይ እንደሚገኝና በተለይ ከ25 እስከ 59 አመት የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ሰዎችን እያጠቃ እንደሚገኝ ያልሸሸጉት ዳይሬክተሩ፤ በፍጥነት ለመሰራጨቱ በምክንያትነት ሊጠቀሱ ከሚችሉት ጉዳዮች መካከል የቫይረሱ አዳዲስ ዝርያዎች በብዛት መፈጠራቸው አንዱ ሊሆን እንደሚችልም ገልጸዋል፡፡

Read 6868 times
Administrator

Latest from Administrator