Print this page
Saturday, 24 April 2021 14:01

ለ30 አመታት የመሯት ዴቢ የተገደሉባትን ቻድ ልጃቸው ይረከቧታል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ቻድን ላለፉት 30 አመታት ያስተዳደሩት ፕሬዚዳንት ኢድሪስ ዴቢ ለ6ኛ ጊዜ በተወዳደሩበት ምርጫ 80 በመቶ ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸውን ይፋ ባደረጉበት ባለፈው ማክሰኞ በአማጺ ሃይሎች በደረሰባቸው ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ፣ የተቋቋመው የአገሪቱ የሽግግር ምክር ቤት በሟቹ ፕሬዚዳንት ወንድ ልጅ ጄኔራል መሃመት ኢድሪስ ዴቢ እንደሚመራ ተነግሯል፡፡
በማዕከላዊ አፍሪካዊቷ አገር ቻድ ቀጣይ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እስኪከናወን አገሪቱን የሚያስተዳድረውንና ለ18 ወራት ይቆያል የተባለውን የሽግግር መንግስት ምክር ቤት የሚመሩት  ባለ አራት ኮከብ ጄነራሉ የ37 አመቱ መሃመት ኢድሪስ ዴቢ፣ ከዚህ ቀደም የአገሪቱ ልዩ ሪፐብሊካን ጋርድ መሪ እንደነበሩም ኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
የምርጫ ውጤቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ በዋና ከተማዋ ኒጃሚና በመንግስትና ውጤቱን በተቃወሙ አማጺያን መካከል ውጊያ መጀመሩን ያስታወሰው ዘገባው፤ ፕሬዝደንት ዴቢ ከአማጺያን ጋር በመዋጋት ላይ የነበሩ ወታደሮችን እየጎበኙ ባሉበት አጋጣሚ በጥይት ተመትተው ህይወታቸው ማለፉንም አክሎ ገልጧል፡፡
የፕሬዚዳንት ዴቢን መገደል ተከትሎ መንግስትና ፓርላማው እንዲበተን የወሰነውና የሽግግር ምክር ቤት ያቋቋመው የአገሪቱ የጦር ሃይል፣ በመላ ቻድ ብሔራዊ ሃዘን ያወጀ ሲሆን፣ ሁሉም ድንበሮች እንዲዘጉ መደረጉንም ዘገባዎች  ያመለክታሉ።

Read 1674 times
Administrator

Latest from Administrator