በመሃመድ ዳውድ ተፅፎ በዘሪሁን አስማማውና በሳሙኤል ደበበ የተዘጋጀው “አየሁሽ” የፍቅር ኮሜዲ ፊልም ነገ ምሽት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ቤት ይመረቃል፡፡ በፊልሙ ራሱ ዘሪሁን አስማማው፣ መኮንን ላዕከ፣ ህሊና ጌታቸው፣ ካሳሁን ፍስሃ (ማንዴላ)፣ ወሳኝነህ ኃይሉ (እሙሹ)፣ ፍሬህይወት ባህሩ፣ ማርታ ካሳ፣ ሮዛ ፈለቀ እና ሌሎች ተውነዋል፡፡ የ90 ደቂቃ ፊልሙን ለመሥራት 8 ወራት የፈጀ ሲሆን ከአዘጋጆቹ ጋር እንድርያስ ተክሉ ፕሮዲዩስ አድርጎታል፡፡