አላቲኖስ የፊልም ሰሪዎች ማህበር ዘንድሮው ለእይታ በበቃው “የመጨረሻዋ ቀሚስ” የተሰኘ ትራጄዲ ፊልም ላይ እንደሚወያይ ማህበሩ አስታወቀ፡፡ በመጪው ሐሙስ ምሽት፣ በሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል በሚቀርበው ዝግጅት ላይ የፊልም ባለሙያዎች፣ “የመጨረሻዋ ቀሚስ” አዘጋጆች እና የጥበቡ አድናቂዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ፊልሙ ለሕዝብ እይታ ከበቃ በኋላ የመጨረሻዎቹ ትዕይንቶች ላይ ለውጥ መደረጉ ይታወቃል፡፡