Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 18 August 2012 13:23

“ዘ ቦርን ሌጋሲ” በአዲስ ተዋናይ ተሳክቶለታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሰሞኑን ለእይታ የበቃው አዲሱ “ዘ ቦርን ሌጋሲ” ፊልም በሰሜን አሜሪካ በመጀመርያ ሳምንቱ 40.3 ሚሊዮን  ዶላር በማስገባት የቦክስ ኦፊስን የገቢ ደረጃ እየመራ ነው፡፡ ላለፈው ሶስት ሳምንት ደረጃውን ተቆጣጥሮ ከቆየው “ዘ ዳርክ ናይት ራይዝስ” መሪነቱን መረከቡ የፊልሙን ምርጥ መሆን ያመለክታል ተብሏል፡፡ የቦርን ፊልሞችን ለመተወን  አዲስ የተመረጠው ጄረሚ ሬነር ሲሆን ተዋናዩ በፊልሙ ላይ ባሳየው ብቃት ቀጣይ ፊልሞችን እንዲሰራ መታጨቱም ተጠቁሟል፡፡ ባለፉት ሶስት የቦርን ተከታታይ ፊልሞች መሪ ተዋናዩ ማት ዴመን እንደነበር አይዘነጋም፡፡

በዋርነር ብሮስ 125 ሚሊዮን ዶላር በጀት ወጥቶበት የተሰራው “ዘ ቦርን ሌጋሲ” ከ “ዘ ዳርክ ናይት ራይዝስ” የሰሜን አሜሪካ ገበያን መንጠቁ ከፍተኛ ተወዳጅነት በማትረፉ ሊሆን ይችላል ተብሏል፡፡ ለእይታ ከበቃ ሶስት ሳምንት ያለፈው “ዘ ዳርክ ናይት ራይዝስ” በሰሜን አሜሪካ ገበያ አራት መቶ ሚሊዮን ዶላር በመላው አለም ደግሞ ስምንት መቶ ሚሊዮን ዶላር እንዳስገባ ታውቋል፡፡ ዋርነር ብሮስ ቀጣይ የቦርን ፊልሞችን በጄረሚ ሬነር ተዋናይነት “ኤ ቦርን ኢዝ ሪስታርትድ” እና “ቦርን ቱቢ ባድ” በሚሉ ርእሶች ለመስራት ይፈልጋል፡፡

 

በሌላ ዜና ማርቭል ስቱዲዮስ የ “ዘ አቬንጀርስ” ፊልምን የመጀመርያ ክፍል ለመስራት እና ለማስተዋወቅ 320 ሚሊዮን ዶላር ወጭ አድርጎ ገቢው በአለም ዙርያ ከ1.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ በመድረሱ ተከታዩን ፊልም ለመስራት እንዳነሳሳው ተገለፀ፡፡ የ “ዘ አቬንጀርስ” ፊልም በቦክስ ኦፊስ የገቢ ደረጃ ታሪክ 3ኛ ደረጃ ላይ እንደተቀመጠ ታውቋል፡፡ የፊልሙ ዲያሬክተርና ደራሲ ጆስ ዌደን ሁለተኛውን የ “ዘ አቬንጀርስ”  ፊልም ለመስራት ጭብጡን እንደጠነሰሰ የገለፀው የኮንታክት ሚውዚክ ዘገባ ሲሆን ከሁለት አመት በኋላ ለእይታ እንደሚያበቃው መግለፁንም አውስቷል፡፡ ፊልሙን በሚቀጥለው አመት ላለመልቀቅ ማርቭል ስቱዲዮ የተገደደው በ “ዘ አቬንጀርስ” ላይ  የሚሰሩ ሱፕር ሂሮዎች በራሳቸው ፊልሞች ሥራ በመጠመዳቸው ነው ተብሏል፡፡

 

 

Read 1563 times Last modified on Saturday, 18 August 2012 13:29