Print this page
Saturday, 27 March 2021 14:04

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

  ምስኪን ሀበሻ፡— አሜን አንድዬ፣ አሜን!
ደህና ሰንብቱልኝማ! የእብዶች ረሀብ

ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ የብርሃን ጭላንጭል ሕዝብ በድንገት ሲያይ
ጨለማውን ለምዶ በእንግዳው ብርሃን ተጨንቆ ሲወያይ
‹ውቃቢ› የሚገፋ ይሆናል ዋና ከልካይ ‹አይሆንም ! ይቅር!› ባይ፤
አዲስ ህልም የሚሸሽ ወትሮም ይቸኩላል አጉል ስም ማውጣት ላይ
 . . .
እውቀት የራበችው ዘርዐ ያዕቆብ ለኢትዮጵያ ውብ እብድ ነበረ፤
ያንቀላፋች መንፈስ ተነስታ እንድትቆም በ‹‹እንዴት?›› የቆፈረ፡፡

ዛሬ ልንኮራበት ያኔ ህዝበ ሮሀ የጉድ ዜና አወጀ፤ዠ
ኪነ-ህንፃ እርቦት ንጉስ ድንጋይ ሊወቅር ስለተዘጋጀ፤
‹‹አለቱን ፈልፍለን ቤተ መቅደስ እና´ርገው ኑ እንነሳ›› ባለ
‹‹ቅዱስ ላልይበላል እኩይ ሀሳብ ያዘ - አበደ!›› ተባለ::
           .    .    .
ሩቅ ዘመንም ሳንሄድ እዚህ ሩብ እልፍ አመት የሆነው ቢጠየቅ. . .
ጦቢያ ተከፋፍሎ  በየጎጥ ተቧድኖ  ሹመት ሲነጣጠቅ፤
ኢትዮጵያን ሊያጸና በአንድነት ሊያቆማት ሲነሳ አባ ታጠቅ፤ዠ
ጠላትን ሊመክት ቴክኖሎጂ ጠምቶት ሴባስቶፖል ሊሰራ፤ዠ
መዶሻ ጨብጦ ጋፋት ውሎ ቢያድር ከቀጥቃጮች ጋራ
ጠይባን ማፍቀሩ የጤና እንዳልሆነ
የአጤ ቴዎድሮስ ነገር ‹‹ማበዱ!›› ተወራ፡፡
.   .   .
ሰላሙ ባልጠራ ውጥንቅጥ እንቅጥቅጥ
አንቀጥቅጥ ዙፋኑ ላፍታ ነግሶ የቆየው፤
ዮሐንስ ብርቱ ባዝኗል
ከአሸንክታብ ፡ ድሪ ማተቡ የፀናን
ክቡር ያገር  ወሰን እንደ እብድ የተራበው፡፡
የፀሐይ ገበታን ትዕምርት ማህተም
በአናቱ ተነቅሶሺህ አመታት የቆየው፤
አለት ያንሳፈፉ እንደ ኑግ ለጥልጠው በእብነ አድማስ የሰፉ
ያያት ቅድማያቶቹ ጥበብ አምድ ሳለው፤
የእጹብ ድንቅ ኪን ፀጋ ቱሩፋት ጌጥ ሀውልት
አክሱም ፊቱ ቆሞዞር ብሎ እንዳይቃኘው፤
የውስጥ ትርምሱየሹመት ሁካታው
ሌቱ ያልተገታ የባእዳን ትንኮሳው ከብቦ ሲያሰቃየው
ፊት ፊቱን ሲያማትር የአገር ድንበር ጥሙ እብደቱ ሲያተከነው ፤
የአዕላፍ ጠይባን ቅርሱን
የምድሩን አንጥረኛ የጥበብ ክህሎት
አንገቱን አዙሮ ቀና ብሎ ሳያየው፤
ዋ! ያ ጀግና ቀረ የጦር ዘመን እጣው
ከክቡር አካሉ አንገቱን ቢለየው ፡፡
.ምኒልክ ተነቅፏል ለእድገት የሚበጁ
የጦቢያን ባለ እጆች መርጦ በማክበሩ፤
ስልጣኔ ተርቦ
ስልክና መኪና ወፍጮና ሲኒማ ሲያስመጣ ላገሩ
ዘመኑን ነቃፊ  ሕዝቡን አወገዙ
‹‹ሰይጣን ሥራ መጣ ! ይኼ እብደት ነው!!›› አሉ፡፡. ..

አዲስ ህልም የሚያልም በዘመኑ እብድ ነው
የህልሙ ፍቺ ሰምሮ በእውን እስከሚያየው፤
ያም ባይሆን እስኪሞት ህልሙን ነው እሚኖረው ፡፡
ስለ ረቂቅ ውበት
ከጊዜያቸው ቀድመው ‹‹እብዶች›› የተባሉ
ዘመናት ተሻግረው
በህያው ግብራቸው ገዝፈው ዛሬም አሉ፤
ያገር አድባር ሆነው
የወል ትውልድን ተስፋ እያቀጣጠሉ፡፡

እዛሬም ላይ ሆነን የምንደመመው፤
‹‹ጉድ›› ተብዬዎቹ
አኑረው ባለፉት ዘመን ተሻጋሪ የ‹‹እብደት  ራዕይ›› ነው፡፡

እኛም...
ብርሃን እየናፈቅን ቆመን እየቃዠን በጨለማ የኖርነው፤
ውብ አለም መድረሻ መንገድ የሚያሳዩን እቡዶች ተርበን ነው፡፡

ሀምሌ 2003 ዓ.ም።
የፀሐይ ገበታ

Read 2790 times
Administrator

Latest from Administrator