Monday, 22 February 2021 08:44

የቄሳርን ለቄሳር

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በእውቀቱ ስዩም


             የድሮ የብሔራዊ ትያትር መርሃግብር
- በመጀመርያ ነቢይ መኮንን ግጥም ያነባል::
- ቀጥሎ ተስፋየ ካሳ አጭር ኮሜዲ ያቀርባል::
- በማስከተል ክበበው ገዳ ፥ የኮንሶ ባህላዊ ውዝዋዜ ያቀርባል( ክቤ ያኔ ተወዛዋዥ ነበር)
- ቀጥሎ ወይዘሮ የዱር ፍሬ፣ 125 ገፅ ያለው አጭር ልቦለድ ያነባሉ ፤
- በመጨረሻ ፊርማዬ አለሙ፣ የፈረመቺበት የግጥም VHS ለሽያጭ ይቀርብና የዝግጅቱ ፍፃሜ ይሆናል፡፡
(ላዲሱ ትውልድ አንባቢ፡- VHS ማለት ከብሉኬት በላይ የሚመዝን የቪድዮ ካሴት ሲሆን አሁን በፍላሽ ዲስክ ተተክቷል፤ ቡሉኬት ራሱ ምን እንደሆነ ማብራራት ይጠበቅብኝ ይሆን?)
ዘንድሮ በብሔራዊ ትያትር
- በመጀመርያ ዲያቆን ዶክተር ገነነ፣ በኢትዮጵያ ትንሳኤ ዙርያ ስብከት ያቀርቡልናል፡፡
-በማስከተል ኡስታዝ ሙሳ፣ ነፍስ እሚያለመልም ትምህርት ይለግሱናል፡፡
-ቀጥሎ፤ አቶ ንጉስ መሳይ፣ የፖለቲካ ፓርቲያቸውን መተዳደርያ ደንብ በስንኝ ያስደምጡናል፡፡ - ለጥቆ ፓስተር ቀልቤሳ ኢጄታ፤ “ አለሌነትና ጦሱ; የሚል ስብከት ይለቁብናል ፡፡
-በመጨረሻ ድምፃዊት ሎዛ “ ነጨኝ በቅበላው ፤ የገጠር ሸበላው; የሚለውን ተወዳጅ ዜማዋን ታቀርብና ፍፃሜ ይሆናል፡፡
ማጠቃለያ መፈክር፤ የእግዜርን ለእግዜር! የቄሳርን ለቄሳር!


Read 3072 times