የሳዑዲ አረቢያው ልዑል መሃመድ ቢን ሰልማን በአገሪቱ ሰሜን ምዕራብ አካባቢ በሚገኘው ኒኦም በረሃ ውስጥ 500 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የሚደረግበት ልዩ ከተማ ሊቆረቁሩ መሆኑን ገልፍ ኒውስ ዘግቧል፡፡
የሃይል አቅርቦቱን ከንጹህ ታዳሽ ሃይል ምንጮች እንደሚያገኝ የተነገረለትና “ዘ ላይን” የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ዘመናዊ ከተማ፣ አንድ ሚሊዮን ያህል ህዝብ እንዲኖርበት መታቀዱንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
አዲሱ የበረሃ ከተማ ምንም አይነት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች እንደማይገቡበት የተነገረ ሲሆን፣ አገሪቱ ኒኦም የተሰኘውን በረሃ ከፍተኛ የቱሪዝም እና የቢዝነስ ማዕከል ልታደርገው ያሰበችው በቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ የሚገኝ ስፍራ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፣ አገሪቱ እ.ኤ.አ በ2030 ከነዳጅ ጥገኝነት ለመላቀቅ ለያዘችው ዕቅድ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ እንደሚጠበቅም አክሎ ገልጧል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል