Saturday, 02 January 2021 10:10

አሃዱ ባንክ ዛሬ መስራች ጉባኤውን ያካሂዳል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

     በ760 ሚሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታል የሚቋቋመው አሃዱ ባንክ ዛሬ በጊዮን ሆቴል መስራች ጉባኤውን ያካሂዳል፡፡
የካቲት 14 ቀን 2012 ዓ.ም ከብሔራዊ ባንክ የመመስረቻ ፍቃድ አግኝቶ በአክስዮን ሽያጭና የምስረታ ሂደት ላይ የቆየው አሃዱ ባንክ፤ በ760 ሚሊዮን ብር የተፈረመ ካፒታልና በ540 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል ዛሬ በይፋ እንደሚቋቋም የአደራጅ ኮሚቴው ሰብሳቢ ኢ/ር ጥጋቡ ሃይለየሱስ ለአዲስ አድማስ ጠቁመዋል፡፡
10 ሺህ 5 መቶ ኢትዮጵያውያንና 190 ትውልደ ኢትዮጵያውያን መስራች የሆኑበት አሀዱ ባንክ፤ በ2025 በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ መሪ ሆኖ ለመውጣት ግብ አስቀምጦ የተመሰረተ ነው ተብሏል።
አሀዱ በባንክ ኢንዱስትሪው ብቁ የባንክ ባለሙያዎች ለማፍራት በዋናነት አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪ ለመደገፍ አልሞ፣ የተቋቋመ መሆኑንም ተመልክቷል፡፡
በዋናነት ማኑፋክቸሪንግ፣ አግሮ ፕሮሰሲንግ በውጭ ንግድ ዘርፍ ከተሰማሩ አካላት ጋርም የመስራት አላማ እንዳለውም ተገልጿል፡፡

Read 1778 times Last modified on Saturday, 02 January 2021 10:24