Sunday, 13 December 2020 00:00

አፍሪካውያ መሪዎች የኢንተርኔት ዋጋን በግማሽ ለመቀነስ ወሰኑ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አማካይነት በአፍሪካ ዘላቂ ማህበረ ኢኮኖሚያዊ እድገት የማምጣት ተልዕኮ አንግቦ  የተቋቋመው ስማርት አፍሪካ አሊያንስ የተባለ አህጉራዊ ጥምረት አባል የሆኑ 30 የአፍሪካ አገራት መሪዎች በኢንተርኔት አገልግሎት ዋጋ ላይ የ50 በመቶ ቅናሽ ለማድረግ መስማማታቸውን ኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
ኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ጋቦን፣ ቡርኪናፋሶ፣ ደቡብ ሱዳንና ማሊን ጨምሮ በአባልነት የተካተቱበት የጥምረቱ አባል አገራት መሪዎች፤ ከመጪው የፈረንጆች አመት ጀምሮ በየአገራቸው የኢንተርኔት አገልግሎት ታሪፍ ላይ የ50 በመቶ ቅናሽ ለማድረግ መወሰናቸውን ባለፈው ሰኞ ባወጡት የጋራ መግለጫ ማስታወቃቸውን ነው ዘገባው ያመለከተው፡፡
በአፍሪካ አገራት የኢንተርኔት ክፍያ እጅግ ከፍተኛ ወይም እጅግ ውድ በመሆኑ ዜጎች የሚፈልጉትንና የሚገባቸውን ያህል የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን እንዳልቻሉ መግባባት ላይ የደረሱት የጥምረቱ አባል ፤ የኢንተርኔት አገልግሎትን ለዜጎች በተመጣጣኝ ክፍያ ለማዳረስ ሲሉ የዋጋ ቅናሹን ለማድረግ መስማማታቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ በመላው አለም እጅግ ውድ የሞባይል ኢንተርኔት ክፍያ የሚጠየቀው በአፍሪካ እንደሆነ ኢኮ ባንክ በ2018 ያወጣውን አለማቀፍ ሪፖርት ጠቅሶ ያስታወሰው ዘገባው፣ ከአፍሪካ ከፍተኛ ክፍያ በሚጠየቅባቸው ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ ዚምቧቡዌና ስዋዚላንድ ለአንድ ጊጋ ባይት ኢንተርኔት ከ20 ዶላር በላይ እንደሚከፈልም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1523 times