ሰዓሊ ኪሩቤል መልኬ “ከእኔ እስከ ቤቴ” በሚል ርዕስ ያዘጋጀው የስዕል ዓውደ ትርዒት ሰኞ በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴስ ይከፈታል።
በአውደ ርዕዩ መግለጫ ላይ እንዳሰፈረው በስራዎቹ የአልባሳትን ታሪካዊ አመጣጥ ለማሳየት አይምክርም፡፡ ይልቁንም ከዚህ ሰፊ ታሪክ ውስጥ ጨርቅ እንዴት የሥነ-ጥበብ አንድ ዘርፍ ሆኖ እንደመጣ ትንሽ ታሪካዊ ዳራውን ጥቆማ በመስጠት ከሥዕል ሥራው ጋር ያለውን ሐሣብ ያይዛል፡፡ ጨርቅን ከቀለም ጋር ወይም ከሌላ ቁስ ጋር በማዋቀርና በማዋሀድ የሚሰራውን፤ “Quilt Art” በመባል የሚታወቀውን ዘርፍ ከራሱ አጋጣሚ በማዛመድ የሚያሳይበት መሆኑንም ባዘጋጀው ፅሁፍ አብራርቷል።
ሰዓሊ ኪሩቤል መልኬ ስለሚያቀርባቸው ሥራዎች ሲገልፅ በተለያዩ ጊዜያትና ሐሳቦች ላይ ተሰርተው የተጠራቀሙ መሆናቸውን ሲጠቅስ
…ቤቴ ሐሳቤ ነው በሚል የስዕሎችን ጉዞ አጠቃሎታል። “ከእኔ እስከ ቤቴ” የሥዕልዓውደ ትርኢት በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሴስ እስከ ታሕሳስ 23 ለዕይታ ይቀርባል።
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና