በመጪው የፈረንጆች 2021 ዓመት ለዓለማቀፍ ጉብኝት ምቹ ናቸው ከተባሉ የዓለማችን 21 ከተሞች መካከል የአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ አንዷ ሆና ተመረጠች
መቀመጫውን በኒውዮርክ ያደረገውና `Conde Nast traveler የተሰኘውና ትኩረቱ አለማቀፍ ቱሪዝም አተኩሮ መፅሔት ከትናንት በስቲያ ይፋ ባደረገው የ2021 ምርጥ የአለም የቱሪዝም ተመራጭ 21 ከተሞች የዘረዘረ ሲሆን በዚሁ ዝርዝር አዲስ አበባ ጨምሮ ሶስት የአፍሪካ ከተሞች ተመራጭ ሆነዋል፡፡ እነሱም የጋናዋ አክራና የአንጎላ ሉዋንዳ ናቸው፡፡
ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የዓለማቀፍ የሰላም ሽልማቶች ማሸነፋቸውን ተከትሎ የሃገሪቱ የቱሪዝም አቅም በ48.6 በመቶ መጨመሩን ያመለከተው የመፅሄቱ ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ በዩኒስኮ ከተመዘገቡ ዘጠኝ አለማቀፍ ቅርሶች ይጠቀሳል፡፡
የአንድነት ፓርክ በአዲስ አበባ ተመራጭ የቱሪስቶች መዳረሻ እንደሚሆን በውስጡ የሚጎበኙ ነገሮች በዝርዝር በማስቀመጥ ነው መፅሔቱ ያወሳው፡፡
በከተማዋ አዲስ የተከፈተው የቢላል ሀበሻ የማህበረሰብ ሙዚየምን ጨምሮ የተለያዩ ሚዚየሞች በአዲስ አበባ ለጉብኝት ተመራጭ እንደሚሆኑ በመፅሔቱ ተመልክቷል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድም ምቹ በሆነው አገልግሎቱ ቱሪዝሙን በእጅጉ እንደሚደግፍ ነው በሪፖርቱ የተመለከተው፡፡
በዚሁ የ21 ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ ከተሞች ዝርዝር ውስጥ ሜክሲኮ፣ ካሊፎርኒያ፣ ኒውዘርላንድ፣ ፣ኪዮቶ፣ኒውዮርክ፣መኖቫ፣ካናዳ፣ ኦስሎ ተካተዋል፡፡