ዱም ሚዲያ እና ፕሮሞሽን ያዘጋጀው “ክብር ለአባትነት” አባቶች የተዘከሩበት ዝግጅት ባለፈው ሰኞ ምሽት በብሔራዊ ትያትር ቀረበ፡፡ አባቶችን ጋቢ በማልበስና እንደ ጥንት ልማድ እግር በማጠብ የደመቀው ዝግጅት ገጣሚ ጌትነት እንየው፣ ትዕግስት ማሞ እና ሌሎችምግጥሞቻቸውንእንዳቀረቡና ቋሚ የአባቶች ቀን መጠየቃቸውን እንዲሁም የማህበራቸው የበላይ ጠባቂ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ መሆናቸውን ማወቅ ተችሏል፡፡