Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 04 August 2012 11:29

ፀረ ኦባማ ዶክመንተሪ ተሰራ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በፀረ ኦባማ አጀንዳዎች የታጀበ ጥናታዊ ፊልም ባለፈው ሳምንት በሰሜን አሜሪካ መታየት ጀመረ፡፡ “2016 ኦባማስ አሜሪካ” በሚልርእስ የተሰራውና የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ በድጋሚ ተመርጠው ለሁለተኛ የስራ ዘመን በዋይት ሃውስ መቆየታቸውን ይቃወማል የተባለው ዶክመንተሪ፤ በገቢ ስኬታማ ሊሆን ባይችል እንኳን በምርጫ ዘመቻቸው ላይ ተፅእኖ እንደሚፈጥር የፎክስኒውስዘገባአመልክቷል፡፡የፊልሙ ዲያሬክተር “ዘ ሩትስ ኦፍ ኦባማስሬጅ” የተባለና በኒዮርክ ታይምስ ምርጥ ሽያጭ አግኝቷል በተባለው መፅሃፍ ደራሲ ዳኒሽ ዴሱዛ የተሰራ ሲሆን ፕሮዲውሰሩ ኦስካር ተሸላሚው ጄራልድ ዋልት እንደሆነ ታውቋል፡፡

የፊልሙ ዲያሬክተር ዴ ሱዛ፤ በናይሮቢ ጎስቋላ መንደሮች የሚኖረውን ደሃውን ጆርጅ የተባለና በእናቱ የሚዛመደውን የኦባማ ወንድም ቃለምልልስ ያደረገለት ሲሆን አሜሪካ ባራክ ኦባማን በድጋሚ ከመረጠች ምን ክፉ እጣ እንደሚገጥማት በሚያሳዩ ትእይንቶች መታጀቡን ፎክስ ኒውስ አብራርቷል፡፡ በፀረ ኦባማ እንቅስቃሴ የተፈረጀው ዶክመንታሪው፤ ሰሞኑን በሰሜን አሜሪካ 400 ሲኒማ ቤቶች መታየት የጀመረ ሲሆን በገቢው እየተሳካለት ግን አይደለም፡፡ በፖለቲካ ጭብጦች የሚሰሩ ዶክመንታሪዎችን ለሲኒማው ኢንዱስትሪ በማስተዋወቅ ፈርቀዳጅ የተባለው በፀረ ጆርጅ ቡሽ ፊልሙ ከፍተኛ እውቅና ያገኘው ማይክል ሙር ሲሆን በ2004 እ.ኤ.አ ለእይታ የበቃለት ዶክመንታሪ በዓለም ዙርያ እስከ 141 ሚሊዮን ዶላር ማስገኘቱ ይታወሳል፡፡

 

 

 

 

Read 1396 times Last modified on Saturday, 04 August 2012 11:33